የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ኤክስፖው በኢትዮጵያ በግንባታና ኮንስትራክሽን ዘርፍ ተግባራዊ እየተደረጉ ያሉ አዳዲስ አሰራሮችና ቴክኖሎጂዎች ለማስተዋወቅ ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር ነው

Jun 25, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሰኔ 17/2017(ኢዜአ)፦የምስራቅ አፍሪካ መሠረተ ልማት እና የውሃ ኤክስፖ በኢትዮጵያ በግንባታና ኮንስትራክሽን ዘርፍ ተግባራዊ እየተደረጉ ያሉ አዳዲስ አሰራሮችን እና ቴክኖሎጂዎች ለማስተዋወቅ ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር መሆኑን የከተማ እና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ገለጹ፡፡

ሚኒስትሯ ለ3ኛ ጊዜ ከሰኔ 19 እስከ 21 ቀን 2017 ዓም ድረስ በሚሊኒየም አዳራሽ የሚካሄደውን የምስራቅ አፍሪካ መሠረተ ልማት እና የውሃ ኤክስፖን በተመለከተ ለመገናኛ ብዙሃን ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በማብራሪያቸውም ባለፉት የለውጥ ዓመታት በኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ዘርፉን ለማሳደግ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል።

ይህም ለአገሪቱ ዕድገት ትልቅ መነቃቃትን የፈጠረ እና ተወዳዳሪነትን በተግባር ማሳየት የቻለ መሆኑን ተናግረዋል።

ኤክስፖው በአገሪቱ እያደገ የመጣውን የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ለመደገፍ በእጅጉ የሚያግዝ ነው ብለዋል።

በኢትዮጵያ በግንባታና ኮንስትራክሽን ዘርፍ ላይ ተግባራዊ እየተደረጉ ያሉ አዳዲስ አሰራሮችና ቴክኖሎጂዎች ለማስተዋወቅ ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥርም አንስተዋል።


በኤክስፖው በኮንስትራክሽንና ግንባታ ዘርፍ የተሰማሩና ከ20 አገራት የተወጣጡ ከ180 በላይ የሚሆኑ ተሳታፊዎች ምርቶቻቸውን ይዘው እንደሚቀርቡ ጠቁመዋል።

ይህም በዘርፉ ከአገራት ጋር የሚፈጠረውን የንግድና መሠል የገበያ ትስስር ለማጠናከር ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥርም አክለዋል።

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚፈጠር የስራ እድል ማስፋትና አካታች ልማትን እውን ማድረግ የኤክስፖው አንዱ ዓላማ መሆኑንም ሚኒስትሯ አብራርተዋል።

ኤክስፖው የአገራትን ልምድና ተሞክሮ ለመቅሰም፣ አስተማማኝ የመሠረተ ልማት ግንባታን ተግባራዊ ለማድረግ፣ የተቀናጀ የከተማ መሠረተ ልማትን ለማረጋገጥ እና በቤት ልማት ዘርፍ አዳዲስና ዘመናዊ አሰራሮችን ለመተግበር ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለው ታምኖበታል።

በተጨማሪም በኮንስትራክሽን ዘርፍ በአገር አቀፍ ደረጃ ተግባራዊ እየተደረጉ ያሉ ስትራቴጂዎችን በተገቢው መልኩ ስራ ላይ ለማዋል አስቻይ ሁኔታን ይፈጥራል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026