የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ኤክስፖው በኢትዮጵያ በግንባታና ኮንስትራክሽን ዘርፍ ተግባራዊ እየተደረጉ ያሉ አዳዲስ አሰራሮችና ቴክኖሎጂዎች ለማስተዋወቅ ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር ነው

Jun 25, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሰኔ 17/2017(ኢዜአ)፦የምስራቅ አፍሪካ መሠረተ ልማት እና የውሃ ኤክስፖ በኢትዮጵያ በግንባታና ኮንስትራክሽን ዘርፍ ተግባራዊ እየተደረጉ ያሉ አዳዲስ አሰራሮችን እና ቴክኖሎጂዎች ለማስተዋወቅ ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር መሆኑን የከተማ እና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ገለጹ፡፡

ሚኒስትሯ ለ3ኛ ጊዜ ከሰኔ 19 እስከ 21 ቀን 2017 ዓም ድረስ በሚሊኒየም አዳራሽ የሚካሄደውን የምስራቅ አፍሪካ መሠረተ ልማት እና የውሃ ኤክስፖን በተመለከተ ለመገናኛ ብዙሃን ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በማብራሪያቸውም ባለፉት የለውጥ ዓመታት በኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ዘርፉን ለማሳደግ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል።

ይህም ለአገሪቱ ዕድገት ትልቅ መነቃቃትን የፈጠረ እና ተወዳዳሪነትን በተግባር ማሳየት የቻለ መሆኑን ተናግረዋል።

ኤክስፖው በአገሪቱ እያደገ የመጣውን የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ለመደገፍ በእጅጉ የሚያግዝ ነው ብለዋል።

በኢትዮጵያ በግንባታና ኮንስትራክሽን ዘርፍ ላይ ተግባራዊ እየተደረጉ ያሉ አዳዲስ አሰራሮችና ቴክኖሎጂዎች ለማስተዋወቅ ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥርም አንስተዋል።


በኤክስፖው በኮንስትራክሽንና ግንባታ ዘርፍ የተሰማሩና ከ20 አገራት የተወጣጡ ከ180 በላይ የሚሆኑ ተሳታፊዎች ምርቶቻቸውን ይዘው እንደሚቀርቡ ጠቁመዋል።

ይህም በዘርፉ ከአገራት ጋር የሚፈጠረውን የንግድና መሠል የገበያ ትስስር ለማጠናከር ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥርም አክለዋል።

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚፈጠር የስራ እድል ማስፋትና አካታች ልማትን እውን ማድረግ የኤክስፖው አንዱ ዓላማ መሆኑንም ሚኒስትሯ አብራርተዋል።

ኤክስፖው የአገራትን ልምድና ተሞክሮ ለመቅሰም፣ አስተማማኝ የመሠረተ ልማት ግንባታን ተግባራዊ ለማድረግ፣ የተቀናጀ የከተማ መሠረተ ልማትን ለማረጋገጥ እና በቤት ልማት ዘርፍ አዳዲስና ዘመናዊ አሰራሮችን ለመተግበር ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለው ታምኖበታል።

በተጨማሪም በኮንስትራክሽን ዘርፍ በአገር አቀፍ ደረጃ ተግባራዊ እየተደረጉ ያሉ ስትራቴጂዎችን በተገቢው መልኩ ስራ ላይ ለማዋል አስቻይ ሁኔታን ይፈጥራል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026