የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በክልሉ በግብርናው ዘርፍ እየተመዘገቡ ያሉ ስኬቶችን የማስቀጠሉ ተግባር ይጠናከራል- እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

Jun 25, 2025

IDOPRESS

ሆሳዕና ፤ ሰኔ 18/2017(ኢዜአ)፡- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርናው ዘርፍ እየተመዘገቡ ያሉ ተስፋ ሰጪ ስኬቶችን የማስቀጠሉ ተግባር በተቀናጀ መንገድ እንደሚጠናከር የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶር) ገለጹ፡፡

"የግብርና ሴክተር ምሶሶዎችን በማሳካት የበለፀገ ቤተሰብ ለማየት እተጋለሁ" በሚል መሪ ሀሳብ በግብርና ትራንስፎርሜሽን አቅጣጫዎች ዙሪያ ለግብርና ልማት ሰራተኞች የተዘጋጀ ስልጠና በሆሳዕና ከተማ ተሰጥቷል፡፡


የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው (ዶር) በወቅቱ እንደተናገሩት፤ የሀገር ኢኮኖሚን ለማሳደግ ትኩረት ከተሰጣቸው አምስት ዘርፎች መካከል አንደኛው ግብርና ነው፡፡

ግብርናን ለማዘመን የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርትና ምርታማነትን መጨመር ላይ ትኩረት ተሰጥቶታል ብለዋል፡፡

የግብርናው ዘርፍ ሁሉን አቀፍ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ስለመሆኑ ጠቁመዋል፡፡

በክልሉ ቀደም ሲል በተከናወኑ የግብርና ልማት ስራዎች ተስፋ ሰጪ ስኬቶች እየተመዘገቡ መሆናቸውን አንስተው፤የበለጠ ለማጠናከር በተቀናጀ መንገድ እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡


ለዚህም ክልሉ ያለውን መሬት በወቅት ሳይገደብ በአግባቡ በማልማት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የግብርና ልማት ባለሙያው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ስሩር በበኩላቸው፤ የግብርና ዘርፍ ከድህነት የመውጫ መንገዳችን ነው ብለዋል፡፡


በክልሉ በግብርናው ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶች እንዲጠናከሩ በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡

በስልጠናው ከሀድያ ዞን የተውጣጡ የግብርና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026