የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በዞኑ በሽታን ተቋቁመው በአጭር ጊዜ ምርት የሚሰጡ የተሻሻሉ የቡና ችግኞች በመተከል ላይ ይገኛሉ

Jun 27, 2025

IDOPRESS

ጊምቢ፤ ሰኔ 19/2017 (ኢዜአ)፦ በምዕራብ ወለጋ ዞን በ66 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ በሽታን ተቋቁመው በአጭር ጊዜ ምርት መስጠት የሚችሉ የተሻሻሉ የቡና ችግኞች ተከላ በመከናወን ላይ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

የጽህፈት ቤቱ ቡና ልማትና ጥራት ቡድን መሪ አቶ ኤፍሬም መስፍን እንዳሉት፤ በዞኑ የተሻሻሉና በአጭር ጊዜ ምርት የሚሰጡ የቡና ችግኞች ተከላ እየተካሄደ ነው።


በዞኑ የቡና ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ በርካታ ተግባራት በመከናወን ላይ መሆኑን ገልጸው፤ በተለይም ያረጁ የቡና ተክሎች የተነቀሉበት ቦታን ጨምሮ በ66 ሺህ ሄክታር አዲስ መሬት ላይ የቡና ችግኝ ተከላ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል።


በአካባቢው ዘንድሮ የዝናብ ስርጭት አነስተኛ በመሆኑ ተከላው ዘግይቶ መጀመሩን የተናገሩት አቶ መስፍን ስራው በተጠናከረ መልኩ በመከናወን ላይ ነው ብለዋል።

የቡና ችግኞቹ በሽታን የመቋቋም አቅም ያላቸውና ከሁለት እስከ ሶስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ምርት የሚሰጡ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡

በተለይም ባለፉት ዓመታት ያረጁ የቡና ዛፎችን በማንሳት በተሻሻሉ ዝርያዎች የመተካት ተግባር በስፋት መከናወኑንም ገልጸዋል።

በዞኑ ከ650 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በቡና ልማት የተሸፈነ ሲሆን ዘንድሮ የሚተከሉ የቡና ችግኞች ሽፋኑን ወደ 700 ሺህ ሄክታር መሬት ለማሳደግ ያግዛል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026