የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በዞኑ በሽታን ተቋቁመው በአጭር ጊዜ ምርት የሚሰጡ የተሻሻሉ የቡና ችግኞች በመተከል ላይ ይገኛሉ

Jun 27, 2025

IDOPRESS

ጊምቢ፤ ሰኔ 19/2017 (ኢዜአ)፦ በምዕራብ ወለጋ ዞን በ66 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ በሽታን ተቋቁመው በአጭር ጊዜ ምርት መስጠት የሚችሉ የተሻሻሉ የቡና ችግኞች ተከላ በመከናወን ላይ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

የጽህፈት ቤቱ ቡና ልማትና ጥራት ቡድን መሪ አቶ ኤፍሬም መስፍን እንዳሉት፤ በዞኑ የተሻሻሉና በአጭር ጊዜ ምርት የሚሰጡ የቡና ችግኞች ተከላ እየተካሄደ ነው።


በዞኑ የቡና ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ በርካታ ተግባራት በመከናወን ላይ መሆኑን ገልጸው፤ በተለይም ያረጁ የቡና ተክሎች የተነቀሉበት ቦታን ጨምሮ በ66 ሺህ ሄክታር አዲስ መሬት ላይ የቡና ችግኝ ተከላ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል።


በአካባቢው ዘንድሮ የዝናብ ስርጭት አነስተኛ በመሆኑ ተከላው ዘግይቶ መጀመሩን የተናገሩት አቶ መስፍን ስራው በተጠናከረ መልኩ በመከናወን ላይ ነው ብለዋል።

የቡና ችግኞቹ በሽታን የመቋቋም አቅም ያላቸውና ከሁለት እስከ ሶስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ምርት የሚሰጡ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡

በተለይም ባለፉት ዓመታት ያረጁ የቡና ዛፎችን በማንሳት በተሻሻሉ ዝርያዎች የመተካት ተግባር በስፋት መከናወኑንም ገልጸዋል።

በዞኑ ከ650 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በቡና ልማት የተሸፈነ ሲሆን ዘንድሮ የሚተከሉ የቡና ችግኞች ሽፋኑን ወደ 700 ሺህ ሄክታር መሬት ለማሳደግ ያግዛል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026