የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ፖርቹጋል ፖርቶ አዲስ በረራ ጀመረ

Jul 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሰኔ 25/2017(ኢዜአ):-የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ፖርቹጋል ፖርቶ አዲስ በረራ ጀምሯል።

አየር መንገዱ ወደ ፖርቶ በሣምንት አራት ጊዜ በረራ እንደሚያደርግ ተገልጿል።

አየር መንገዱ ወደ ፖርቹጋል ፖርቶ ከተማ የሚያደርገውን በረራ አስመልክቶ ዛሬ ማምሻውን የማስጀመሪያ መርኃ ግብር ተከናውኗል።

በመርኃ ግብሩ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው፣ በኢትዮጵያ የፖርቹጋል አምባሳደር ልዊሳ ፍራጎሶ እንዲሁም ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው በዚሁ ጊዜ፥ አየር መንገዱ ወደ ፖርቶ የሚያደርገው በረራ ፖርቹጋልን ከአፍሪካ ጋር ለማስተሳሰር እንደሚያግዝ ተናግረዋል።

ወደ አውሮፓ ለሚጓዙ መንገደኞች የተቀላጠፈ አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያስችለውም ነው የገለጹት።

በኢትዮጵያ የፖርቹጋል አምባሳደር ልዊሳ ፍራጎሶ በበኩላቸው፥ ኢትዮጵያ እና ፖርቹጋል ረዥም ዘመናትን ያስቆጠረ ወዳጅነት እንዳላቸው ተናግረዋል።

አየር መንገዱ ወደ ፖርቶ የጀመረው በረራም የሀገራቱን ወዳጅነት በኢኮኖሚና ህዝብ ለህዝብ ትስስር ለማጠናከር እንደሚያግዝም አውስተዋል።

አየር መንገዱ ዛሬ ያስጀመረውን በረራ ጨምሮ ከ145 በላይ ዓለም አቀፍ መዳረሻዎችን እየሸፈነ ይገኛል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ2035 ዓመታዊ ገቢውን ወደ 25 ቢሊዮን ዶላር ከፍ ለማድረግና በዓመት 67 ሚሊዬን መንገደኞችን ለማጓጓዝ ራዕይ አስቀምጦ እየሰራ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.