የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ፖርቹጋል ፖርቶ አዲስ በረራ ጀመረ

Jul 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሰኔ 25/2017(ኢዜአ):-የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ፖርቹጋል ፖርቶ አዲስ በረራ ጀምሯል።

አየር መንገዱ ወደ ፖርቶ በሣምንት አራት ጊዜ በረራ እንደሚያደርግ ተገልጿል።

አየር መንገዱ ወደ ፖርቹጋል ፖርቶ ከተማ የሚያደርገውን በረራ አስመልክቶ ዛሬ ማምሻውን የማስጀመሪያ መርኃ ግብር ተከናውኗል።

በመርኃ ግብሩ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው፣ በኢትዮጵያ የፖርቹጋል አምባሳደር ልዊሳ ፍራጎሶ እንዲሁም ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው በዚሁ ጊዜ፥ አየር መንገዱ ወደ ፖርቶ የሚያደርገው በረራ ፖርቹጋልን ከአፍሪካ ጋር ለማስተሳሰር እንደሚያግዝ ተናግረዋል።

ወደ አውሮፓ ለሚጓዙ መንገደኞች የተቀላጠፈ አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያስችለውም ነው የገለጹት።

በኢትዮጵያ የፖርቹጋል አምባሳደር ልዊሳ ፍራጎሶ በበኩላቸው፥ ኢትዮጵያ እና ፖርቹጋል ረዥም ዘመናትን ያስቆጠረ ወዳጅነት እንዳላቸው ተናግረዋል።

አየር መንገዱ ወደ ፖርቶ የጀመረው በረራም የሀገራቱን ወዳጅነት በኢኮኖሚና ህዝብ ለህዝብ ትስስር ለማጠናከር እንደሚያግዝም አውስተዋል።

አየር መንገዱ ዛሬ ያስጀመረውን በረራ ጨምሮ ከ145 በላይ ዓለም አቀፍ መዳረሻዎችን እየሸፈነ ይገኛል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ2035 ዓመታዊ ገቢውን ወደ 25 ቢሊዮን ዶላር ከፍ ለማድረግና በዓመት 67 ሚሊዬን መንገደኞችን ለማጓጓዝ ራዕይ አስቀምጦ እየሰራ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026