የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን እስከ መስከረም ድረስ 17 እናደርሳለን - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

Jul 4, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን እስከ መስከረም ድረስ 17 እናደርሳለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ሙስናን በተመለከተ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በማብራሪያቸውም መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን እስከ መስከረም ድረስ 17 እናደርሳለን ብለዋል።

ኢትዮጵያ ውስጥ መንግስታዊ ሙስና የለም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ነገር ግን ከአገልግሎት አንጻር ትናንሽ የሙስና ተግባራት አሉ ብለዋል።

ይህን ለማስተካከል ወደ ስራ የገባው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በሶስት ወራት ብቻ 23 ተቋማትን በማካተት 124 አገልግሎቶችን እየሰጠ መሆኑን ገልጸዋል።

አሁን አንድ ማዕከል ብቻ ነው ያለው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እስከ መስከረም ድረስ 17 እናደርሳለን መሶብ እየተስፋፋ አገልግሎት እየዘመነ ሲሄድ የእጅ በእጅ ሙስና እየቀነሰ ይሄዳል ሲሉም አስታውቀዋል።

ከዚያ ውጭ ሙስናን መፀየፍ የግለሰቦችን አመለካከትና ውሳኔን የሚጠይቅ መሆኑንም ማወቅ ይገባል ነው ያሉት።

ሙስናን የምንከላከለው በስርዓት ነው፤ በዘረጋነው የመሶብ ስርዓትም ተገልጋዮች ከ90 በመቶ በላይ እርካታ አሳይተዋል ይህንን በሁሉም አካባቢዎች ማስፋት ከተቻለ ሙስና በእጅጉ ይቀንሳል ብለዋል በማብራሪያቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.