የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በዞኑ በበልግ እርሻ በዘር ከተሸፈነው 368 ሺህ ሄክታር መሬት 8 ነጥብ 7 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ይጠበቃል

Jul 4, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦በምዕራብ ጉጂ ዞን በበልግ እርሻ በዘር ከተሸፈነው 368 ሺህ ሄክታር መሬት 8 ነጥብ 7 ሚሊዮን ኩንታል ምርት እንደሚጠበቅ የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ።

በኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ የተመራ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች ቡድን በምዕራብ ጉጂ ዞን እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎችን እየጎበኘ ነው።

በዚህም በምዕራብ ጉጂ ዞን ሱሮ በርጉዳ ወረዳ በክላስተር የለማ ስንዴ እና ጤፍ ጎብኝቷል።


የምዕራብ ጉጂ ዞን ግብርና ጽህፈት ቤት ሃላፊ ቱኬ አና ለከፍተኛ የስራ ሀላፊዎቹ በሰጡት ማብራሪያ፤ በዞኑ በተያዘው የክረምት ወራት 368ሺህ ሄክታር መሬት በተለያዩ የዘር ዓይነት መሸፈኑን ገልጸዋል።

እነኚህም በቆሎ፣ ስንዴ፣ ቦሎቄ፣ ጤፍ፣ ማሾ እና ሌሎችም መሆኑን ጠቁመው፤ ከዚህም 8 ነጥብ 7 ሚሊዮን ኩንታል ምርት እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።

የአርሶ አደሩ የሥራ ባህል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መሆኑንም አንስተዋል።


ምርታማነት እንዲያድግም መንግስት የተለያዩ ድጋፎችን እያደረገ መሆኑን ጠቁመው ምርጥ ዘር፣ ማዳበሪያ እና ሌሎች ግብዓቶችን ማቅረቡንም ተናግረዋል።

በምዕራብ ጉጂ ዞን እየተካሄደ በሚገኘው የልማት ስራዎች ጉብኝት የክልሉ ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳን ጨምሮ በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ከፍያለው ተፈራ እንዲሁም ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026