የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በክልሉ በቴክኖሎጂ የታገዘ የፍርድ አሰጣጥ ሂደት ተግባራዊ ሆኗል

Jul 30, 2025

IDOPRESS

አሶሳ፤ ሐምሌ 20/2017 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የፍርድ አሰጣጥ ሂደት ተግባራዊ መደረጉን የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ሰንበታ ቀጄላ ተናገሩ።

የክልሉ ምክርቤት ጉባዔ በሁለተኛ ቀን ውሎው የክልሉን ጠቅላይ ፍርድ ቤት የ2017 በጀት ዓመት ሪፖርት በማድመጥ ላይ ነው።


ሪፖርቱን ያቀረቡት የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ፕሬዚዳንት ሰንበታ ቀጄላ እንደተናገሩት፤ ተገልጋዮች የተቀላጠፈ አገልግሎት እንዲያገኙ ለማስቻል ችሎቶችን በቴክኖሎጂ በመታገዝ በማከናወን ላይ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በዚህም 57 ባለጉዳዮች ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ባዘጋጀው የቪዲዮ ኮንፈረንስ በርቀት የሙግት ክርክር እንዲያገኙ መደረጉን ለአብነት አንስተዋል።

መዝገቦችን ከብልሽት ለመታደግም ወደ ሶፍት ኮፒ የመቀየር ስራ መጀመሩን የተናገሩት ፕሬዝዳንቱ፤ ይህም የፍርድ ቤቱን የውሳኔ ጥራት የሚያሳድግ እና ከተገልጋዮችም አመኔታን የሚያስገኝ ነው ብለዋል።

አክለውም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በክልሉ 18ሺህ 405 መዛግብት የፍርድ ውሳኔ ማግኘታቸውን ገልጸዋል።

ፍርድ ቤቱ ከዳኝነት አገልግሎት 12 ሚሊዮን 813 ሺህ ብር ገቢ ማግኘቱንም ፕሬዝዳንቱ ገልጸዋል።


ምክር ቤቱ በትናንትናው ዕለት የክልሉን አስፈፃሚ ተቋማት እና የምክር ቤቱን ሪፖርት መርምሮ ያፀደቀ ሲሆን በዛሬው ዕለት ደግሞ የክልሉን ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ሪፖርት፣ የክልሉ የመንግስት ሰራተኞች አዋጅ እና ሌሎች አጀንዳዎች ላይ እንደሚመክር ይጠበቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.