
አሶሳ፤ ሐምሌ 20/2017 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የፍርድ አሰጣጥ ሂደት ተግባራዊ መደረጉን የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ሰንበታ ቀጄላ ተናገሩ።
የክልሉ ምክርቤት ጉባዔ በሁለተኛ ቀን ውሎው የክልሉን ጠቅላይ ፍርድ ቤት የ2017 በጀት ዓመት ሪፖርት በማድመጥ ላይ ነው።

ሪፖርቱን ያቀረቡት የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ፕሬዚዳንት ሰንበታ ቀጄላ እንደተናገሩት፤ ተገልጋዮች የተቀላጠፈ አገልግሎት እንዲያገኙ ለማስቻል ችሎቶችን በቴክኖሎጂ በመታገዝ በማከናወን ላይ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በዚህም 57 ባለጉዳዮች ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ባዘጋጀው የቪዲዮ ኮንፈረንስ በርቀት የሙግት ክርክር እንዲያገኙ መደረጉን ለአብነት አንስተዋል።
መዝገቦችን ከብልሽት ለመታደግም ወደ ሶፍት ኮፒ የመቀየር ስራ መጀመሩን የተናገሩት ፕሬዝዳንቱ፤ ይህም የፍርድ ቤቱን የውሳኔ ጥራት የሚያሳድግ እና ከተገልጋዮችም አመኔታን የሚያስገኝ ነው ብለዋል።
አክለውም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በክልሉ 18ሺህ 405 መዛግብት የፍርድ ውሳኔ ማግኘታቸውን ገልጸዋል።
ፍርድ ቤቱ ከዳኝነት አገልግሎት 12 ሚሊዮን 813 ሺህ ብር ገቢ ማግኘቱንም ፕሬዝዳንቱ ገልጸዋል።

ምክር ቤቱ በትናንትናው ዕለት የክልሉን አስፈፃሚ ተቋማት እና የምክር ቤቱን ሪፖርት መርምሮ ያፀደቀ ሲሆን በዛሬው ዕለት ደግሞ የክልሉን ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ሪፖርት፣ የክልሉ የመንግስት ሰራተኞች አዋጅ እና ሌሎች አጀንዳዎች ላይ እንደሚመክር ይጠበቃል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026