
አሶሳ፤ ሐምሌ 20/2017 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የፍርድ አሰጣጥ ሂደት ተግባራዊ መደረጉን የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ሰንበታ ቀጄላ ተናገሩ።
የክልሉ ምክርቤት ጉባዔ በሁለተኛ ቀን ውሎው የክልሉን ጠቅላይ ፍርድ ቤት የ2017 በጀት ዓመት ሪፖርት በማድመጥ ላይ ነው።

ሪፖርቱን ያቀረቡት የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ፕሬዚዳንት ሰንበታ ቀጄላ እንደተናገሩት፤ ተገልጋዮች የተቀላጠፈ አገልግሎት እንዲያገኙ ለማስቻል ችሎቶችን በቴክኖሎጂ በመታገዝ በማከናወን ላይ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በዚህም 57 ባለጉዳዮች ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ባዘጋጀው የቪዲዮ ኮንፈረንስ በርቀት የሙግት ክርክር እንዲያገኙ መደረጉን ለአብነት አንስተዋል።
መዝገቦችን ከብልሽት ለመታደግም ወደ ሶፍት ኮፒ የመቀየር ስራ መጀመሩን የተናገሩት ፕሬዝዳንቱ፤ ይህም የፍርድ ቤቱን የውሳኔ ጥራት የሚያሳድግ እና ከተገልጋዮችም አመኔታን የሚያስገኝ ነው ብለዋል።
አክለውም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በክልሉ 18ሺህ 405 መዛግብት የፍርድ ውሳኔ ማግኘታቸውን ገልጸዋል።
ፍርድ ቤቱ ከዳኝነት አገልግሎት 12 ሚሊዮን 813 ሺህ ብር ገቢ ማግኘቱንም ፕሬዝዳንቱ ገልጸዋል።

ምክር ቤቱ በትናንትናው ዕለት የክልሉን አስፈፃሚ ተቋማት እና የምክር ቤቱን ሪፖርት መርምሮ ያፀደቀ ሲሆን በዛሬው ዕለት ደግሞ የክልሉን ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ሪፖርት፣ የክልሉ የመንግስት ሰራተኞች አዋጅ እና ሌሎች አጀንዳዎች ላይ እንደሚመክር ይጠበቃል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026