🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መስከረም 30/2018 (ኢዜአ)፡- አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻ ልማት ስራዎች የቱሪስት ፍሰቱን ከመጨመር ባሻገር በዘርፉ ከፍተኛ የገበያ አቅም እየፈጠሩ እንደሚገኙ የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ።
ስድስተኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፌዴሬሽን ምክር ቤት አምስተኛ ዓመት የሥራ ዘመን የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም መካሄዱ ይታወሳል።
የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በመክፈቻ ስነ ሥርዓቱ መንግስት የኢትዮጵያን ዘላቂ እድገት ለማረጋገጥ በ2018 በጀት ዓመት በልዩ ልዩ መስኮች የያዛቸውን እቅዶች ለሁለቱ ምክር ቤቶች አቅርበዋል።
በንግግራቸው መንግሥት ባለፉት ዓመታት የቱሪዝም ዘርፉን ለማሳደግ ትኩረት በመስጠት አዝጋሚ የነበረውን ጉዞ ወደ ጉልህ የእድገት አንቀሳቃሽ ሞተር መለወጥ መቻሉን ተናግረዋል።
በበጀት ዓመቱ የተዋበች ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚያስችሉ የቱሪዝም መዳረሻዎችን የማስፋፋት ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።
የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ እንደገና አበበ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንዳሉት መንግስት ቱሪዝምን እንደ ትልቅ የኢኮኖሚ መስክ በመውሰድ ዘርፉን የሚያነቃቁ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል።
ኢትዮጵያ በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ሃብቶች የታደለች ብትሆንም ዘርፉ ለረጅም ዘመናት ተገቢውን ትኩረት ሳያገኝ በመቆየቱ በአግባቡ ሳትጠቀምበት ቀርታለች።
ባለፉት የለውጥ ዓመታት ለዘርፉ እድገት ማነቆ የሆኑ ተግዳሮቶችን በመፍታት ሀገሪቱ ከዘርፉ የሚገባትን ጥቅም እንድታገኝ ልዩ ትኩረት በመስጠት እየተሰራበት ይገኛል ብለዋል።
በተለይም ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን ሀብት ለማስተዋወቅ የሚያግዝ የቱሪዝም ስትራቴጂ ማዘጋጀቷ በመስኩ በርካታ ለውጦች እንዲመዘገቡ ማስቻሉን አንስተዋል።
አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎችን የማልማት እና ነባር የቱሪስት መስህቦችን የማደስና የመንከባከብ ስራ መሰራቱንም ጠቅሰዋል።
ይህም የጎብኚዎችን ፍላጎት በማሳደግ ኢትዮጵያ ከዘርፉ የምታገኘው ገቢ እንዲያድግ ማድረጉን ገልጸዋል።
የሀገር ውስጥ ቱሪዝምን ማስፋፋትና ከአፍሪካ ሃገራት የሚደረጉ የቱሪስት ፍሰቶችን ማሳደግ ተገቢ መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታው እንደገና አበበ (ዶ/ር) ጠቁመዋል።
በቀጣይ ኢትዮጵያን የሚያቋርጡ ተጓዥችን በስቶፕ ኦቨር (የእግረ መንገድ ቱሪዝም) በመጠቀም ከቱሪዝም የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026