የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በደሴ ከተማ የቱሪስት መዳረሻ ሥፍራዎችን በማልማት ለቱሪስቶች ምቹ የማድረግ ተግባር በስፋት እየተከናወነ ነው

Oct 13, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ደሴ ፤ ጥቅምት 1/2018 (ኢዜአ)፡-በደሴ ከተማ የቱሪስት መዳረሻ ሥፍራዎችን በማልማት ለቱሪስቶች ምቹ የማድረግ ተግባር በስፋት እየተከናወነ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ አስታወቀ።

በደሴ ከተማ "ቱሪዝም ለዘላቂ ልማት" በሚል መሪ ሀሳብ የዓለም የቱሪዝም ቀን ለ33ኛ ጊዜ በተለያዩ ዝግጅቶች ተከብሯል።


የመምሪያው ኃላፊ ወይዘሮ ትዕግስት አበበ በዝግጅቱ ላይ እንደገለፁት፣ በከተማው የቱሪስት መዳረሻ ሥፍራዎችን በማልማት ለቱሪስቶች ምቹ የማድረግ ተግባር በስፋት እየተከናወነ ነው።


በዚህም የደሴ ሙዚዬምን በማደስ፣ የአይጠየፍ አዳራሽ እና የመርሆ ቤተ መንግስታትን ለጎብኚዎች ምቹ በማድረግ ዘርፉ እንዲነቃቃ የማድረግ ስራ መሰራቱን ገልጸዋል።

ለዚህምየቱሪስቶችና የጎብኝዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱንና የቆይታ ጊዜያቸውን በማራዘም ውጤት እየተገኘ መሆኑን አስረድተዋል።


የወሎን የአብሮነት፣ የመቻቻል፣ የፍቅርና የሰላም ተምሳሌትነት በተግባር በማሳየት ወሎን የማስተዋወቅ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የደሴ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሰይድ የሱፍ በበኩላቸው በከተማው የሚገኙ የቱሪስት መዳረሻ ሥፍራዎችን በማልማት የቱሪዝም ዘርፉን ለማነቃቃት እየተሰራ ነው።


አሁን ላይ ባለ 5 ኮከብ እና ዘመናዊ ሆቴሎች፣ የእንግዳ ማረፊያዎችና ሌሎች የአገልግሎት መስጫ ተቋማት እየተገነቡ መሆኑን አስረድተዋል።

በቱሪዝም ቀን አከባበር ስነ ስርዓቱ ላይ አመራሮች፣ የቱሪዝም ባለሙያዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.