የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በወላይታ ሶዶ ከተማ አርሶ አደሮች ተደራጅተው በእንስሳትና መኖ ልማት የጀመሩት ሥራ ተሞክሮ የሚወሰድበት ነው

Oct 15, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ወላይታ ሶዶ ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ):-በወላይታ ሶዶ ከተማ አርሶ አደሮች ተደራጅተው በእንስሳትና መኖ ልማት የጀመሩት ሥራ ተሞክሮ የሚወሰድበት ነው ሲሉ የተለያዩ ክልሎች የዘርፉ ባለሙያዎች ተናገሩ።

በከተማው ስር የሚገኙ አርሶ አደሮች በመንደር ተደራጅተው በእንስሳትና መኖ ልማት የጀመሩት ሥራ የሌማት ትሩፋት ኢንሼቲቭን የሚያጠናክር መሆኑም ተመልክቷል።

የግብርና ሚኒስቴር ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ጋር በመተባበር የእንስሳትና ዓሣ ሀብት ኤክስቴንሽን ምርጥ ተሞክሮን ለመቅሰም ያለመ ሀገራዊ የልምድ መለዋወጫ የመስክ ጉብኝት አካሂዷል።

በመስክ ጉብኝቱ ላይ የተሳተፉት የተለያዩ ክልሎች የዘርፉ ባለሙያዎች እንደገለጹት፣ በከተማው አርሶ አደሮች በመንደር ተደራጅተው በእንስሳትና መኖ ልማት የጀመሩት ሥራ ውጤታማና በአርአያነት የሚወሰድ መሆኑን ተናግረዋል።


አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ ባለሙያዎች መካከል በአማራ ክልል ግብርና ቢሮ የእንስሳት ሀብት ልማት ባለሙያ አቶ ጌትነት አየሁ እንደገለጹት በከተማው የወተት መንደርን በመፍጠር አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ለማድረግ የተሰራው ሥራ የሚደነቅ ነው።

በተለይ በእንስሳት መኖ ልማት ዘርፍ ያዩትን ተሞክሮ ወደክልላቸው ወስደው በማስፋት የአርሶ አደሮችን ህይወት ለመቀየር እንደሚሰሩ ገልጸዋል።

በኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ የእንስሳት ሀብት ልማት ባለሙያ መሠረት ከበደ በበኩላቸው በመስክ ጉብኝቱ ላይ ለሌሎች አርሶ አደሮች ተሞክሮ የሚሆን ልምድ መቅሰማቸውን ተናግረዋል።


በወላይታ ሶዶ ከተማ አርሶ አደሮች በመንደር ተደራጅተው በእንስሳትና መኖ ልማት የጀመሩት ሥራ በሌማት ትሩፋት ኢንሼቲቭ አተገባበር ላይ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣቱን አንስተው ይህም ተሞክሮ ማስፋት እንደሚገባም አመልክተዋል።

የመስክ ጉብኝቱ የተሻለ ልምድ ለማግኘት አስችሎናል ያሉት ደግሞ በጎፋ ዞን ግብርና መምሪያ የእንስሳት እና ዓሣ ሀብት ልማት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሙሉቀን ተመስገን ናቸው።


የወተት ልማትን ከመኖ ልማት ለይቶ ማየት እንደማይቻል ጠቁመው፣ በአንድ አርሶ አደር ከ2 ነጥብ 5 ሄክታር በላይ የመኖ ሣር እየለማ ማየታቸው ለስራው የተሰጠውን ትኩረት ያሳያል ብለዋል።

የእንስሳት እርባታ ሥራው ሳይንሱን የተከተለ መሆኑ ደግሞ አርሶ አደሩን ይብልጥ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026