🔇Unmute
ባሕርዳር ፤ ጥቅምት 4/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ከ2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት በመመደብ የመንገድ ግንባታና ጥገና ስራዎች ለማከናወን ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ አስታወቀ።
በክልሉ በተያዘው በጀት ዓመት የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎችን በማከናወን የልማት ትስስሩንና የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ይገኛል።
የአማራ ክልል ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ቀለሙ ሙሉነህ በተለይ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በተያዘው በጀት ዓመት በ34 ፕሮጀክቶች ከ102 ኪሎ ሜትር በላይ የአዳዲስ መንገዶች ግንባታ እንዲሁም የ6 ሺህ 38 ኪሎ ሜትር የነባር መንገዶች ጥገና ለማድረግ ታቅዷል።
ለዚህም ከክልሉ 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር እና ከፌዴራል መንገድ ፈንድ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ደግሞ ከ1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት ተይዞ የመንገድ ግንባታ ስራዎች ለማከናወን ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
በመንገድ ግንባታው የ91 አነስተኛ፣ መካከለኛና ከፍተኛ ድልድዮች ግንባታ የሚካሄድ መሆኑን ጠቁመው፤ መሰረተ ልማቱ ዞን፣ወረዳና ቀበሌዎችን የሚያገናኝ ይሆናል ብለዋል።
በግንባታው ከ20 ሺህ 200 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026