የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በአማራ ክልል ከ2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት የመንገድ ግንባታና ጥገና ስራዎች ለማከናወን ዝግጅት እየተደረገ ነው

Oct 15, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ባሕርዳር ፤ ጥቅምት 4/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ከ2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት በመመደብ የመንገድ ግንባታና ጥገና ስራዎች ለማከናወን ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ አስታወቀ።

በክልሉ በተያዘው በጀት ዓመት የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎችን በማከናወን የልማት ትስስሩንና የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ይገኛል።

የአማራ ክልል ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ቀለሙ ሙሉነህ በተለይ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በተያዘው በጀት ዓመት በ34 ፕሮጀክቶች ከ102 ኪሎ ሜትር በላይ የአዳዲስ መንገዶች ግንባታ እንዲሁም የ6 ሺህ 38 ኪሎ ሜትር የነባር መንገዶች ጥገና ለማድረግ ታቅዷል።

ለዚህም ከክልሉ 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር እና ከፌዴራል መንገድ ፈንድ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ደግሞ ከ1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት ተይዞ የመንገድ ግንባታ ስራዎች ለማከናወን ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

በመንገድ ግንባታው የ91 አነስተኛ፣ መካከለኛና ከፍተኛ ድልድዮች ግንባታ የሚካሄድ መሆኑን ጠቁመው፤ መሰረተ ልማቱ ዞን፣ወረዳና ቀበሌዎችን የሚያገናኝ ይሆናል ብለዋል።

በግንባታው ከ20 ሺህ 200 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026