የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በጉራጌ ዞን የመስህብ ሥፍራዎችን በማልማትና በማስተዋወቅ የተጀመሩ ተግባራት ውጤት እያመጡ ነው 

Oct 15, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ወልቂጤ ፤ ጥቅምት 5/2018 (ኢዜአ):- በጉራጌ ዞን የቱሪዝም መስህብ ሥፍራዎችን በማልማትና በማስተዋወቅ ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ውጤት እያመጡ መሆኑን የዞኑ ባሕልና የቱሪዝም መምሪያ አስታወቀ ።

ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ሃላፊ መሠረት አመርጋ፤ ዞኑ ካላው እምቅ የቱሪዝም አቅምና መዳረሻዎች አንፃር ይገኝ የነበረው ጥቅም አነስተኛ ሆኖ መቆየቱን አስታውሰዋል።


ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ይህን መቀየር የሚያስችል ሥራ በተቀናጀና ባለድርሻ አካላትን ባሳተፈ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም በዞኑ ያሉ የተፈጥሮ፣ ሰው ሰራሽና እና ታሪካዊ የመሥህብ ሥፍራዎችን በማልማትና በማስተዋወቅ ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ማሳደግ መቻሉን ገልጸዋል ።

በተለይም በዞኑ ያሉ የቱሪዝም መሥህቦችን ለማስተዋወቅ እና ለማስጎብኘት ከግሉ ዘርፍ፣ ከመገናኛ ብዙኃንና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት መሰራቱ ውጤት እያመጣ መሆኑን ተናግረዋል።


በዘንድሮው የመስቀል በዓል ከሃገር ውስጥ እና ከተለያዩ ዓለም ሃገራት በርካታ ጎብኚዎች ወደ ዞኑ መምጣታቸውን ጠቅሰው፤ በዚህም 230 ሚሊዮን ብር ገቢ መገኘቱን አንስተዋል ።

ከውጭ የሚመጡ ጎብኚዎች የ"ጀፎረ" የገጠር ኮሪደር ልማት ላይ የብስክሌት ሽርሽር ማድረግ እየተለመደ መምጣቱ እና በየአካባቢውም የሕዝቡ እንግዳ ተቀባይነት የቱሪስቱን የቆይታ ጊዜ ለማራዘም እያስቻለ እንደሆነም ጠቅሰዋል።


በዚህም የእደ ጥበብ ወጤቶች ተፈላጊነት መጨመር እና ለአገልግሎት ሰጪ ተቋማት መነቃቃት መፍጠሩን አውስተው፤ ለቱሪስቶች ማረፊያ የሚሆኑ የሆቴሎችና ሌሎች አመቺ ሥፍራዎችን የማስፋፋት ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን ገልጸዋል።


ዞኑ በዘርፉ ካለው አቅም አንጻር ብዙ ሊሰራ እንደሚገባ ያነሱት ሃላፊዋ፤ ለዚህም ይረዳ ዘንድ አዳዲስ የመሥህብ ሥፍራዎችን የማልማትና የማስተዋወቅ እንዲሁም መሰረት ልማት የማሟላት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አስረድተዋል ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026