የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በምዕራብ ሸዋ ዞን ከ31 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የለማ ሰብል እየተሰበሰበ ነው

Oct 17, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አምቦ፤ጥቅምት 6/2018(ኢዜአ) ፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን በመኸሩ ከ31 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ ለምቶ የደረሰ ሰብል በመሰብሰብ ላይ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

በጽህፈት ቤቱ የአፈር ልማት ማሻሻያ ቡድን መሪ አቶ ተክሌ ኢዶሳ ለኢዜአ በሰጡት ማብራሪያ የመኸሩ የግብርና ልማት በጥሩ ሁኔታ ላይ በመሆኑ የተሻለ ምርት የሚጠበቅበት ነው ብለዋል።


በዞኑ 31 ሺህ 28 ሄክታር መሬት ላይ የለማውና የደረሰው ሰብል አሁን በመሰብሰብ ላይ መሆኑን አንስተው ከዚህም ከ938 ሺህ 490 ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።

በመኸሩ የስንዴ፣ ገብስ፣ ባቄላ፣ ቦሎቄና ሌሎችም ሰብሎች በመድረሳቸው በመሰብሰብ ላይ መሆናቸውን ገልጸው ከሰብል ስብሰባው ጎን ለጎን የአፈሩን እርጥበት በመጠቀም ዳግም የማልማት የዝግጅት ስራ የተጀመረባቸው አካባቢዎች አሉ ብለዋል።

የመኸር ምርቱ በተሰበሰበባቸው አካባቢዎችም እስካሁን ከ6 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች የመሸፈን ስራ መከናወኑን ገልጸዋል።

የተሰበሰበውን ሰብል ማሳ እርጥበቱ ሳይጠፋ ዳግም በዘር የመሸፈን ስራው ውጤታማ እንዲሆን ዘመናዊ ማረሻዎች ተሰራጭተው ጥቅም ላይ እንዲውሉ መደረጉንም አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.