🔇Unmute
አምቦ፤ጥቅምት 6/2018(ኢዜአ) ፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን በመኸሩ ከ31 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ ለምቶ የደረሰ ሰብል በመሰብሰብ ላይ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
በጽህፈት ቤቱ የአፈር ልማት ማሻሻያ ቡድን መሪ አቶ ተክሌ ኢዶሳ ለኢዜአ በሰጡት ማብራሪያ የመኸሩ የግብርና ልማት በጥሩ ሁኔታ ላይ በመሆኑ የተሻለ ምርት የሚጠበቅበት ነው ብለዋል።

በዞኑ 31 ሺህ 28 ሄክታር መሬት ላይ የለማውና የደረሰው ሰብል አሁን በመሰብሰብ ላይ መሆኑን አንስተው ከዚህም ከ938 ሺህ 490 ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።
በመኸሩ የስንዴ፣ ገብስ፣ ባቄላ፣ ቦሎቄና ሌሎችም ሰብሎች በመድረሳቸው በመሰብሰብ ላይ መሆናቸውን ገልጸው ከሰብል ስብሰባው ጎን ለጎን የአፈሩን እርጥበት በመጠቀም ዳግም የማልማት የዝግጅት ስራ የተጀመረባቸው አካባቢዎች አሉ ብለዋል።
የመኸር ምርቱ በተሰበሰበባቸው አካባቢዎችም እስካሁን ከ6 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች የመሸፈን ስራ መከናወኑን ገልጸዋል።
የተሰበሰበውን ሰብል ማሳ እርጥበቱ ሳይጠፋ ዳግም በዘር የመሸፈን ስራው ውጤታማ እንዲሆን ዘመናዊ ማረሻዎች ተሰራጭተው ጥቅም ላይ እንዲውሉ መደረጉንም አስረድተዋል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026