የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በምዕራብ ሸዋ ዞን ከ31 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የለማ ሰብል እየተሰበሰበ ነው

Oct 17, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አምቦ፤ጥቅምት 6/2018(ኢዜአ) ፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን በመኸሩ ከ31 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ ለምቶ የደረሰ ሰብል በመሰብሰብ ላይ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

በጽህፈት ቤቱ የአፈር ልማት ማሻሻያ ቡድን መሪ አቶ ተክሌ ኢዶሳ ለኢዜአ በሰጡት ማብራሪያ የመኸሩ የግብርና ልማት በጥሩ ሁኔታ ላይ በመሆኑ የተሻለ ምርት የሚጠበቅበት ነው ብለዋል።


በዞኑ 31 ሺህ 28 ሄክታር መሬት ላይ የለማውና የደረሰው ሰብል አሁን በመሰብሰብ ላይ መሆኑን አንስተው ከዚህም ከ938 ሺህ 490 ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።

በመኸሩ የስንዴ፣ ገብስ፣ ባቄላ፣ ቦሎቄና ሌሎችም ሰብሎች በመድረሳቸው በመሰብሰብ ላይ መሆናቸውን ገልጸው ከሰብል ስብሰባው ጎን ለጎን የአፈሩን እርጥበት በመጠቀም ዳግም የማልማት የዝግጅት ስራ የተጀመረባቸው አካባቢዎች አሉ ብለዋል።

የመኸር ምርቱ በተሰበሰበባቸው አካባቢዎችም እስካሁን ከ6 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች የመሸፈን ስራ መከናወኑን ገልጸዋል።

የተሰበሰበውን ሰብል ማሳ እርጥበቱ ሳይጠፋ ዳግም በዘር የመሸፈን ስራው ውጤታማ እንዲሆን ዘመናዊ ማረሻዎች ተሰራጭተው ጥቅም ላይ እንዲውሉ መደረጉንም አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026