የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በአፋር ክልል የእንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማትን በማዘመን በዘርፉ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ነው

Oct 23, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሰመራ፤ ጥቅምት 12/2018(ኢዜአ)፦ የክልሉን እምቅ የእንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት በማዘመን የዘርፉን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑንየአፋር ክልል የእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።

"በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ትግበራ ክልሉን የቤተሰብ ብልፅግና ተምሳሌት ማድረግ" በሚል መሪ ሐሳብ የአፋር ክልል እንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት ቢሮ እና ተጠሪ ተቋማቱ በሠመራ ከተማ የምክክር መድረክ አካሂደዋል።


የአፋር ክልል እንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም መሐመድ፤ የክልሉን እምቅ የእንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት በማዘመን የዘርፉን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

የዘርፉን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ በማሳደግ የአርብቶ አደሩን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ብዙ ስራዎች መሰራታቸውን አስታውሰው በተለይም የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ብዙዎችን ተጠቃሚ እያደረገ ይገኛል ብለዋል።

በመርሃ ግብሩ የስጋ፣ የወተት፣ የእንቁላልና የማር ምርቶችን ከፍ ማድረግ መቻሉን ገልፀው፤ በዓሳ ሃብትም በተመሣሣይ ለውጦች መመዝገባቸውን ነው ያብራሩት።

የዘርፉን ስኬት ለማጉላት የደረቅ መኖ ዝግጅት ላይ በማተኮር መሰራቱን ሲያነሱ ለአብነትም ባለፈው ዓመት 362 ሺህ ቶን የእንስሳት መኖ ማምረት መቻሉን አብራርተዋል።

በዚህም ባለፉት አምስት ዓመታት በመኖ ዝግጅት ዘርፍ 46 ሺህ አርብቶ አደሮችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል።

በቢሮው የእንስሳት ጤና አገልግሎትና ኢንስፔክሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አብዱልቃድር መሐመድ በበኩላቸው በክልሉ ውስጥ ካሉ ሀብቶች አንዱና ዋነኛው የእንስሳት ሀብት መሆኑን ጠቁመዋል።


የእንስሳቱን ጤንነት በማስጠበቅ ምርታማነታቸውን ለማሳደግ ከአጋር አካላት ጋር መሰራቱን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026