የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በደሴ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተዘጋጀ

Oct 29, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ደሴ ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፡- በደሴ ከተማ አስተዳደር መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለመስጠት ዝግጁ ተደረገ።

ማዕከሉ 16 ተቋማት እና ከ70 በላይ የአገልግሎት ዘርፎች የተመቻቹ ሲሆን፤ ይህም ብልሹ አሰራርን በማስቀረት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንደሚሰጡ ተመላክቷል።

ለአገልግሎት አሰጣጡ ምቹ እንዲሆን በቴክኖሎጂ የተደገፈ የሲስተም ዝርጋታ ስራው የተሳካ ስለመሆኑ በተደረገው የሙከራ ትግበራ ማረጋገጥ ተችሏል።

ለከተማው ማህበረሰብ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈ አገልግሎት በቅርብ ቀናት ወደ ተሟላ ስራ እንደሚገባ ተጠቁሟል።


የደሴ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝን ጨምሮ ሌሎች የከተማ አመራር አባላትና ባለድርሻ አካላት መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከሉን ተመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.