🔇Unmute
ደሴ ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፡- በደሴ ከተማ አስተዳደር መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለመስጠት ዝግጁ ተደረገ።
ማዕከሉ 16 ተቋማት እና ከ70 በላይ የአገልግሎት ዘርፎች የተመቻቹ ሲሆን፤ ይህም ብልሹ አሰራርን በማስቀረት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንደሚሰጡ ተመላክቷል።
ለአገልግሎት አሰጣጡ ምቹ እንዲሆን በቴክኖሎጂ የተደገፈ የሲስተም ዝርጋታ ስራው የተሳካ ስለመሆኑ በተደረገው የሙከራ ትግበራ ማረጋገጥ ተችሏል።
ለከተማው ማህበረሰብ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈ አገልግሎት በቅርብ ቀናት ወደ ተሟላ ስራ እንደሚገባ ተጠቁሟል።

የደሴ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝን ጨምሮ ሌሎች የከተማ አመራር አባላትና ባለድርሻ አካላት መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከሉን ተመልክተዋል።
Jul 17, 2025
Apr 24, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፦ የሲሚንቶ ንግድ እና መሰረታዊ የፍጆታ እቃዎችን በተመለከተ የወጡ መመሪያዎች ገበያውን በማረጋጋትና የዋጋ ግሽበትን በመቀ...
Feb 12, 2025