የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በፌደራል መንግስት ብቻ 26ሺህ 500 ኪሎ ሜትር መንገድ እየተገነባ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

Oct 29, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ በፌደራል መንግስት ብቻ 26ሺህ 500 ኪሎ ሜትር መንገድ እየተገነባ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ እየተካሄደ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛሉ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የፕሮጀክቶች ክትትልን በሚመለከት በሰጡት ማብራሪያ ኢትዮጵያ ውስጥ 346 የመንገድ ፕሮጀክቶች በግንባታ ላይ መሆናቸውን ጠቁመው 26ሺህ 500 ኪሎ ሜትር መንገድ በፌደራል መንግስት ብቻ እየተገነባ ይገኛል ብለዋል።

እነዚህን ሁሉ ፕሮጀክቶች በተመሳሳይ መከታተል እጅግ አስቸጋሪ ስራ መሆኑን ጠቅሰው ግድብን በሚመለከትም ከ200 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው 14 መካከለኛና አነስተኛ የግድብ ፕሮጀክቶች እንዳሉም ገልጸዋል።

መንግስት የማስፈጸም አቅሙን በማሳደግ ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ እየሰራ ነው ሲሉም ተናግረዋል።

ከተረጂነት መላቀቅን በተመለከተ ሲገልጹም ተረጂነት የመስራት ጉልበትን የሚበላ ካንሰር ነው ብለዋል።

በስንዴ፣ ፍራፍሬና ሌማት ትሩፋት የምንሰራው ስራም ከተረጂነት ለመላቀቅ ባለን ቁርጠኝነት ነው ያሉ ሲሆን ስለዚህ ጨከን ብለን ተረጂነት ይበቃናል ማለት አለብን ነው ያሉት።

ደግሞም እንችላለን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እርዳታ ብዙ ጣጣ በውስጡ አለበት ኢትዮጵያን መለመኛ ማድረግ መቆም አለበት ነው ያሉት በማብራሪያቸው።

የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ እድገት በሚመለከትም በኢትዮጵያ የመጣው የእሳቤ ለውጥ በርካታ እምርታዎችን አምጥቷል ብለዋል።

ኢትዮጵያ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ2032 በአፍሪካ 2ኛ፣ በ2036 ደግሞ ከአፍሪካ የመጀመሪያውን ኢኮኖሚ እንደምትገነባ ጥርጥር የለኝም ሲሉ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.