የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የኮሪደር ልማቱ አምቦ ከተማን አዲስና ውብ ገጽታ አላብሷታል 

Oct 31, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አምቦ ፤ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፡- በአምቦ ከተማ የተከናወነው የኮሪደር ልማት ከተማዋን አዲስና ውብ ገጽታ እንዳላበሳት የአምቦ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ።

የኮሪደር ልማት ስራ በስፋት እየተከናወነባቸው ከሚገኙ የኦሮሚያ ክልል ከተሞች መካከል አንዷ የአምቦ ከተማ ናት።


በከተማው የተከናወነውን የኮሪደር ልማት አስመልክቶ ኢዜአ ያነጋገራቸው የአምቦ ከተማ ነዋሪዎች የኮሪደር ልማቱ ከተማዋ በፊት ያላትን ገጽታ እየቀየረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የአምቦ ከተማ ነዋሪ አቶ መንግስቱ ረጋሳ እንዳሉት፤ ኮሪደሩ ከመጀመሩ በፊት ከተማዋን አቋርጦ የሚያልፈው ዋና መንገድ በትራፊክ እና በሰዎች እንቅስቃሴ እጅግ የተጨናነቀ ነበር።


የኮሪደር ልማት ስራው ከተከናወነ ወዲህ ግን መንገዱ እንዲሰፋ በመደረጉ ለተሽከርካሪ እና ለሰዎች እንቅስቃሴ ምቹ ሁኔታ ከመፍጠሩ ባለፈ የከተማዋን ውበት ጨምሯል ብለዋል።

በዋና መንገዱ ግራ እና ቀኝ ሰዎች ያለ ስጋት የእግር ጉዞ እያደረጉበት ጤናቸውን እየጠበቁ መሆኑን መመልከታቸውን ጠቅሰው ወጣቶች የመዝናኛ እና የማረፊያ ስፋራ ማግኘታቸውን ተናግረዋል።


ሌላው የከተማው ነዋሪ አቶ መንጌ ተፈሪ፣ የከተማው ኮሪደር ልማት ሳይጀመር በፊት በመንገድ ዳር ላይ የተከማቹ ደረቅ ቆሻሻዎች መንገድ ላይ ለማለፍ ምቹ ሁኔታ አይፈጥሩም ነበር ብለዋል።


አሁን ላይ ቆሻሻ ስፍራዎቹ ወደ መዝናኛ ቦታነት መቀየራቸውን ተናግረው ለኮሪደር ልማቱ ስኬታማነት ከከተማው አስተዳደር ጎን በመቆም ድጋፋቸውን እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።

በተሰራው የኮሪደር ልማት አካባቢው በንጹህ አየር ስለተሞላ ከተማዋን ለመኖር ምቹ እና ጽዱ አድርጓታል ሲሉም ተናግረዋል።


ወጣት ባይሳ ታምሩ በበኩሉ፤ የሃገር እድገትን ለማፋጠን የወጣቶች ሚና ሰፊ መሆኑን ጠቅሶ፤ በከተማው እየተካሄደ ያለው ልማት እንዲፋጠን በንቃት እንደሚሳተፍ ገልጿል።


የኮሪደር ልማት ስራው የከተማዋን ገፅታ በመቀየር ለቱሪዝምና ኢንቨስትመንት ምቹ እንደሚያደርጋት ገልጾ ከሌሎች ወጣቶች ጋር በመሆን የልማት ስራው እስከሚጠናቀቅ የድራሻውን እንደሚወጣም አረጋግጧል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.