🔇Unmute
ክልል፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ አመት ገበያ ለማረጋጋት በተቀናጀ አግባብ በተሰራ ስራ ውጤት እየተገኘ መሆኑን የክልሉ ንግድ ቢሮ አስታወቀ።
የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ተስፋዬ ገሾ ለኢዜአ እንደተናገሩት በበጀት አመቱ በክልሉ ገበያን ለማረጋጋት አቅርቦትን መጨመርና የቁጥጥርና የክትትል ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
በሩብ ዓመቱም ቢሮው ህገ ወጥ ንግድ መከላከል ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማሳደጊያ ስራ መስራቱን ተናግረዋል።
ህገ ወጥ ንግድን ከመከላከል ጎን ለጎን የምርት ተደራሽነት እንዲሰፋ በማድረግ አቅርቦት እና ፍላጎት እንዲጣጣም ሲሰራ መቆየቱንም አስታውሰዋል።

በዚህም የግብርና ምርቶችንና ለምግብነት የሚውሉ የኢንዱስትሪ ውጤቶችን በብዛት፣ በጥራትና በተመጣጣኝ ዋጋ በቅዳሜና እሁድ ገበያ፣ በባዛርና በኤግዚቢሽን ለህብረተሰቡ እንዲቀርብ መደረጉን ነው የተናገሩት።
እንዲሁም ከባለ ድርሻ አካላት፣ ከዩኒየኖች፣ ከህብረት ስራ ማህበራትና በከተማ ግብርና ላይ ከተሰማሩ አካላት ጋር በመሆን የተሻሉ የአቅርቦት ስራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል።

በክልሉ ባለፉት ሶስት ወራት 19 ተጨማሪ የቅዳሜና እሁድ ገበያዎችን በማቋቋም በአጠቃላይ ወደ 590 ገበያዎች ማድረስ መቻሉን ጠቅሰው በነዚህ አማራጭ ገበያዎች የፍጆታ ምርቶች እንዲቀርቡ በማድረግ ገበያ ማረጋጋት መቻሉን አንስተዋል።
በተለይም የአትክልትና ፍራፍሬ አምራቾች በአቅራቢያቸው በተፈጠረ የገበያ ትስስር ምርቶችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ እያደረጉ በተሻለ መልኩ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።

እንዲሁም በክልሉ ከሚገኙ የምግብና ምግብ ነክ አምራች ኢንዱስትሪዎች ህብረተሰቡ በፋብሪካ ዋጋ ምርት እንዲያገኝ መደረጉን አንስተዋል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026