🔇Unmute
ክልል፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ አመት ገበያ ለማረጋጋት በተቀናጀ አግባብ በተሰራ ስራ ውጤት እየተገኘ መሆኑን የክልሉ ንግድ ቢሮ አስታወቀ።
የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ተስፋዬ ገሾ ለኢዜአ እንደተናገሩት በበጀት አመቱ በክልሉ ገበያን ለማረጋጋት አቅርቦትን መጨመርና የቁጥጥርና የክትትል ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
በሩብ ዓመቱም ቢሮው ህገ ወጥ ንግድ መከላከል ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማሳደጊያ ስራ መስራቱን ተናግረዋል።
ህገ ወጥ ንግድን ከመከላከል ጎን ለጎን የምርት ተደራሽነት እንዲሰፋ በማድረግ አቅርቦት እና ፍላጎት እንዲጣጣም ሲሰራ መቆየቱንም አስታውሰዋል።

በዚህም የግብርና ምርቶችንና ለምግብነት የሚውሉ የኢንዱስትሪ ውጤቶችን በብዛት፣ በጥራትና በተመጣጣኝ ዋጋ በቅዳሜና እሁድ ገበያ፣ በባዛርና በኤግዚቢሽን ለህብረተሰቡ እንዲቀርብ መደረጉን ነው የተናገሩት።
እንዲሁም ከባለ ድርሻ አካላት፣ ከዩኒየኖች፣ ከህብረት ስራ ማህበራትና በከተማ ግብርና ላይ ከተሰማሩ አካላት ጋር በመሆን የተሻሉ የአቅርቦት ስራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል።

በክልሉ ባለፉት ሶስት ወራት 19 ተጨማሪ የቅዳሜና እሁድ ገበያዎችን በማቋቋም በአጠቃላይ ወደ 590 ገበያዎች ማድረስ መቻሉን ጠቅሰው በነዚህ አማራጭ ገበያዎች የፍጆታ ምርቶች እንዲቀርቡ በማድረግ ገበያ ማረጋጋት መቻሉን አንስተዋል።
በተለይም የአትክልትና ፍራፍሬ አምራቾች በአቅራቢያቸው በተፈጠረ የገበያ ትስስር ምርቶችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ እያደረጉ በተሻለ መልኩ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።

እንዲሁም በክልሉ ከሚገኙ የምግብና ምግብ ነክ አምራች ኢንዱስትሪዎች ህብረተሰቡ በፋብሪካ ዋጋ ምርት እንዲያገኝ መደረጉን አንስተዋል።
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...
Apr 14, 2026
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026