የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በኦሮሚያ ክልል ገበያን ለማረጋጋት በተሰራው ስራ ውጤት እየተገኘ ነው

Oct 31, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ክልል፤ ጥቅምት 21/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ አመት ገበያ ለማረጋጋት በተቀናጀ አግባብ በተሰራ ስራ ውጤት እየተገኘ መሆኑን የክልሉ ንግድ ቢሮ አስታወቀ።

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ተስፋዬ ገሾ ለኢዜአ እንደተናገሩት በበጀት አመቱ በክልሉ ገበያን ለማረጋጋት አቅርቦትን መጨመርና የቁጥጥርና የክትትል ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

በሩብ ዓመቱም ቢሮው ህገ ወጥ ንግድ መከላከል ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማሳደጊያ ስራ መስራቱን ተናግረዋል።

ህገ ወጥ ንግድን ከመከላከል ጎን ለጎን የምርት ተደራሽነት እንዲሰፋ በማድረግ አቅርቦት እና ፍላጎት እንዲጣጣም ሲሰራ መቆየቱንም አስታውሰዋል።


በዚህም የግብርና ምርቶችንና ለምግብነት የሚውሉ የኢንዱስትሪ ውጤቶችን በብዛት፣ በጥራትና በተመጣጣኝ ዋጋ በቅዳሜና እሁድ ገበያ፣ በባዛርና በኤግዚቢሽን ለህብረተሰቡ እንዲቀርብ መደረጉን ነው የተናገሩት።

እንዲሁም ከባለ ድርሻ አካላት፣ ከዩኒየኖች፣ ከህብረት ስራ ማህበራትና በከተማ ግብርና ላይ ከተሰማሩ አካላት ጋር በመሆን የተሻሉ የአቅርቦት ስራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል።


በክልሉ ባለፉት ሶስት ወራት 19 ተጨማሪ የቅዳሜና እሁድ ገበያዎችን በማቋቋም በአጠቃላይ ወደ 590 ገበያዎች ማድረስ መቻሉን ጠቅሰው በነዚህ አማራጭ ገበያዎች የፍጆታ ምርቶች እንዲቀርቡ በማድረግ ገበያ ማረጋጋት መቻሉን አንስተዋል።

በተለይም የአትክልትና ፍራፍሬ አምራቾች በአቅራቢያቸው በተፈጠረ የገበያ ትስስር ምርቶችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ እያደረጉ በተሻለ መልኩ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።


እንዲሁም በክልሉ ከሚገኙ የምግብና ምግብ ነክ አምራች ኢንዱስትሪዎች ህብረተሰቡ በፋብሪካ ዋጋ ምርት እንዲያገኝ መደረጉን አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026