የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የኢትዮጵያ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ሀገራዊ እድገትን በማፋጠን ትልቅ ኢኮኖሚ መገንባት የሚያስችሉ ናቸው

Nov 3, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ነቀምቴ፤ ጥቅምት 22/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የወጠነቻቸው ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ሀገራዊ እድገትን በማፋጠን ትልቅ ኢኮኖሚ መገንባት የሚያስችሉ መሆናቸውን ኢዜአ ያነጋገራቸው ምሁራን ገለጹ።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ይፋ የተደረጉት የጉባ ላይ ብስራቶች የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ዕድገት በማሳለጥ የአፍሪካ የብልጽግና ተምሳሌትነቷን እውን የሚያደርጉ እንደሆኑ መገለጹ ይታወሳል።


ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቅርቡ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በሰጡት ማብራሪያ፤ በሂደት ላይ ያሉ እነዚህ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ቀጣይ እጣ ፈንታዋን የሚወስኑ መሆናቸውን አፅንኦት ሰጥተዋል።

በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው በወለጋ ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩ ምሁራን እንዳሉት ኢትዮጵያ የወጠነቻችው ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ከድህነት ለመውጣት የተጀመረውን ጉዞ የሚያፋጥኑ ናቸው።

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጨምሮ በዚህ ዓመት ሥራ የጀመሩና በውጥን ላይ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች ሀገራዊ እድገትን ማፋጠን ብቻ ሳይሆን ሀገራችንን ከአደጉ ሀገራት ተርታ የሚያሰልፉ ናቸው ብለዋል።


በወለጋ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል መምህር ጌታቸው መኛር(ዶ/ር)፤ በመንግስት እየተተገበሩ ያሉ የኢኮኖሚ መዋቅር ለውጦች የኢትዮጵያን ፈጣን እድገት እውን የሚያደርጉ ናቸው ሲሉ ገልጸዋል።

መንግስት ከአነስተኛና መካከለኛ ፕሮጀክቶች በላይ በትላልቅ ፕሮጀክቶች ላይ ማተኮሩ በአጭር ጊዜ ከድህነት ለመውጣት መንገድ የሚጠርግ መሆኑንም ተናግረዋል።

በተለይም መንግስት ኢትዮጵያ ያላትን እምቅ ሀብት በመለየት እንደየ አስፈላጊነቱ ወደ ልማት መግባቱ አዲስ ልምምድ መሆኑን አስታውሰው፣ ጅምር እንቅስቃሴው መሰረታዊ እድገትን ማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።

አሁን በተጀመረው አካሄድ በሁሉም ዘርፍ ያሉትን አቅሞች አሟጦ በመጠቀም የዜጎችን ተጠቃሚነት የማረጋገጡ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አመልክተዋል።

ግዙፍ መሰረታዊ ፕሮጀክቶቹ የሀገርን ብሔራዊ ገፅታ የሚቀይሩ መሆኑን ጠቅሰው ይህም ዓለም አቀፋዊ ተቀባይነቷን በማሳደግ ተፅእኖ ፈጣሪነቷን ያጎላል ብለዋል።


ሌላው በዩኒቨርሲቲው የኢኮኖሚክስ መምህር የሆኑት ገመቹ ሙላቱ(ዶ/ር) በበኩላቸው የግዙፍ ፕሮጀክቶች ግንባታ ለሀገርና ለዜጎች ዘርፈ ብዙ ትሩፋት ይዘው ይመጣሉ ነው ያሉት።

በተለይም ከሥራ ዕድል ፈጠራ አንጻር ጉልህ ድርሻ እንዳላቸው ገልጸው፣ ወጣትና አምራች የሆነውን የሰው ሀይል ውጤታማ ለማድረግ ያግዛል ብለዋል።

ከሁሉም በላይ እነዚህ የልማት ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን ፈጣን የእድገት ጉዞ በማስቀጠል ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባት የሚያስችሉ መሆናቸውን አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026