🔇Unmute
ደብረ ብርሃን ፤ ጥቅምት 25/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን 44 ሺህ ሄክታር መሬት በበጋ መስኖ ስንዴ ለማልማት ተግባራዊ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።
መምሪያው የበጋ የመስኖ ልማት ማስጀመሪያ የንቅናቄ መድረክ በአንጎለላና ጠራ ወረዳ አካሂዷል።
የዞኑ ግብርና መምሪያ አቶ ታደሰ ማሙሻ በወቅቱ እንደገለጹት፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የዞኑን የምግብ ሉአላዊነት ከማረጋገጥ ባሻገር ለገበያ የሚሆን ለማምረት ትኩረት ተሰጥቷል።
ለዚህም 44 ሺህ ኼክታር መሬት በበጋው ወራት በመስኖ ስንዴ ለማልማት ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን አስረድተዋል።
በአርሶ አደሮች ተሳትፎ በመስኖ ከሚለማው መሬት 1 ነጥብ 6 ሚሊየን ኩንታል ስንዴ በማምረት ለኢንዱስትሪ ግብአትና ገበያን ለማረጋጋት መታቀዱን ተናግረዋል።
ባለፉት የለውጥ ዓመታት አርሶ አደሩ የዝናብ ወቅትን ሳይጠብቅ ባሉ የውሃ አማራጮች መስኖን በመጠቀም ስንዴን በዓመት ሁለት ጊዜ በማምረት የምግብ ዋስትናውን እያረጋገጠ መሆኑን ገልጸዋል።
ምርታማነትን ይበልጥ ለማሳደግም መንግስት የአፈር ማዳበሪያና ምርጥ ዘር በወቅቱ እያሰራጨና የግብርና ባለሙያዎች ድጋፍ እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል።
በዞኑ የሲያ ደብርና ዋዩ ወረዳ ግብርና ጽሕፈት ቤት ሀላፊ አቶ ጥላሁን እንዳላማው ፤ በወረዳው 850 ሄክታር መሬት በበጋ መስኖ ለማልማት ወደ ተግባር መገባቱን ገልጸዋል።
በወረዳው ከ1 ሺህ ሄክታር የሚበልጥ መሬት በበጋ መስኖ ስንዴ እንደሚለማ የተናገሩት ደግሞ የአሳግርት ወረዳ ግብርና ጽሕፈት ቤት ሀላፊ አቶ ወሰኔ አምበርብር ናቸው።
እቅዱን ለማሳካትም የመሬት ልየታ፣ የውሃ መሳቢያ ሞተር አቅርቦትና ሌሎች ዝግጅቶች ተጠናቀው ተግባራዊ ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉን አስረድተዋል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026