የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በምዕራብ ጎንደር ዞን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴን ለማነቃቃት እየተሰራ ነው

Nov 6, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ገንዳውኃ፤ጥቅምት 26/2018(ኢዜአ)፦በምዕራብ ጎንደር ዞን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴን ለማነቃቃት እየተሰራ መሆኑን የዞኑ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ አስታወቀ።

አበዳሪ ተቋማትን፣ የኢንቨስትመንት ፎካሎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈና ዘርፉን ለማነቃቃት ያለመ የምክክር መድረክ በገንዳውኃ ከተማ ዛሬ ተካሄዷል።

በዞኑ የኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ መሰንበት መልካሙ እንደገለጹት በዞኑ በጸጥታ ችግር ምክንያት ተቀዛቅዞ የቆየውን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ለማነቃቃት እየተሰራ ነው።

ዞኑ ለኢንቨስትመንት ምቹ የሆነ ሰፋፊ መሬትና ተስማሚ የአየር ንብረት እንዳለው ገልፀው የዛሬው መድረክም በአካባቢው የሰፈነውን ሰላም ተከትሎ አዳዲስ አልሚዎችን ለመሳብና ነባር ኢንዱስትሪ ዘርፉን ለማነቃቃት የብድር አቅርቦትና ሌሎች ችግሮችን ለመፍታት በማለም መሰናዳቱን አብራርተዋል።

የገንዳ ውኃ ኢንዱስትሪ ፓርክ ልማት ኮርፖሬሽን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ተወካይ ኃላፊ አቶ ታድሎ አቡሃይ እንዳሉት በከተማው 134 ሄክታር የሚጠጋ ቦታ ለኢንዱስትሪ ፓርክ ተለይቶ መሰረተ ልማት የማሟላት ስራ ተሰርቷል።

እስካሁን ከ14 በላይ የሚሆኑ ባለሀብቶች ማሸነሪ በመትከል እየሰሩ እንደሚገኙ ጠቁመው ወደ ስራ ያልገቡትን በመደገፍ ወደ ተግባር ለማስገባት ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል።

በምዕራብ ጎንደር ዞን የዋሊያ ካፒታል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ ብርሃኑ ስመኘው በበኩላቸው በዞኑ የሚካሄደውን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ለመደገፍ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም ለአልሚ ባለሃብቶች የግብርና ግብዓቶችን፣ የሰሊጥ ማበጠሪያና ዘመናዊ መውቂያ ማሽኖች እየቀረበ እንደሚገኝ ጠቁመው በቀጣይም ፍላጎትን መሰረት ያደረገ የካፒታል እቃዎች ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የገንዳውኃ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ አቶ ደመወዝ ምትኩ በበኩላቸው የአካባቢውን ፀጋ ለማልማትና ሰፊ የስራ እድል ለመፍጠር ብድር በማቅረብ እየሰሩ መሆናቸውን አስረድተዋል።

በውይይቱ ላይም አመራሮች፣ ባለሃብቶችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት መሳተፋቸውም ተመልክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026