🔇Unmute
ገንዳውኃ፤ጥቅምት 26/2018(ኢዜአ)፦በምዕራብ ጎንደር ዞን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴን ለማነቃቃት እየተሰራ መሆኑን የዞኑ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ አስታወቀ።
አበዳሪ ተቋማትን፣ የኢንቨስትመንት ፎካሎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈና ዘርፉን ለማነቃቃት ያለመ የምክክር መድረክ በገንዳውኃ ከተማ ዛሬ ተካሄዷል።
በዞኑ የኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ መሰንበት መልካሙ እንደገለጹት በዞኑ በጸጥታ ችግር ምክንያት ተቀዛቅዞ የቆየውን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ለማነቃቃት እየተሰራ ነው።
ዞኑ ለኢንቨስትመንት ምቹ የሆነ ሰፋፊ መሬትና ተስማሚ የአየር ንብረት እንዳለው ገልፀው የዛሬው መድረክም በአካባቢው የሰፈነውን ሰላም ተከትሎ አዳዲስ አልሚዎችን ለመሳብና ነባር ኢንዱስትሪ ዘርፉን ለማነቃቃት የብድር አቅርቦትና ሌሎች ችግሮችን ለመፍታት በማለም መሰናዳቱን አብራርተዋል።
የገንዳ ውኃ ኢንዱስትሪ ፓርክ ልማት ኮርፖሬሽን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ተወካይ ኃላፊ አቶ ታድሎ አቡሃይ እንዳሉት በከተማው 134 ሄክታር የሚጠጋ ቦታ ለኢንዱስትሪ ፓርክ ተለይቶ መሰረተ ልማት የማሟላት ስራ ተሰርቷል።
እስካሁን ከ14 በላይ የሚሆኑ ባለሀብቶች ማሸነሪ በመትከል እየሰሩ እንደሚገኙ ጠቁመው ወደ ስራ ያልገቡትን በመደገፍ ወደ ተግባር ለማስገባት ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል።
በምዕራብ ጎንደር ዞን የዋሊያ ካፒታል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ ብርሃኑ ስመኘው በበኩላቸው በዞኑ የሚካሄደውን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ለመደገፍ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም ለአልሚ ባለሃብቶች የግብርና ግብዓቶችን፣ የሰሊጥ ማበጠሪያና ዘመናዊ መውቂያ ማሽኖች እየቀረበ እንደሚገኝ ጠቁመው በቀጣይም ፍላጎትን መሰረት ያደረገ የካፒታል እቃዎች ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የገንዳውኃ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ አቶ ደመወዝ ምትኩ በበኩላቸው የአካባቢውን ፀጋ ለማልማትና ሰፊ የስራ እድል ለመፍጠር ብድር በማቅረብ እየሰሩ መሆናቸውን አስረድተዋል።
በውይይቱ ላይም አመራሮች፣ ባለሃብቶችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት መሳተፋቸውም ተመልክቷል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026