የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በሚዛን አማን ከተማ በሁለተኛው ምዕራፍ ከ4 ኪሎ ሜትር በላይ የተቀናጀ የኮሪደር ልማት ሥራ እየተፋጠነ ነው

Nov 7, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሚዛን አማን ፤ ጥቅምት 27/2018(ኢዜአ)፦የሚዛን አማን ከተማን ገጽታ ይበልጥ የሚያጎላ ከ4 ኪሎ ሜትር በላይ የተቀናጀ የኮሪደር ልማት ሥራ እየተፋጠነ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ።

በሀገሪቱ ዜጎችን ለመጪው ዘመን የከተሜነት ኑሮ ማዘጋጀትን ታሳቢ አድርጎ የተጀመረው የኮሪደር ልማት የበርካታ ከተሞችን ገጽታ በመለወጥ ለኑሮ ምቹና ሳቢ እንዲሁም ተወዳዳሪ እንዲሆኑ እያስቻለ ነው።


በበርካታ ከተሞች ተግባራዊ የሆነው የኮሪደር ልማት ከገጽታ ግንባታ ባሻገር የትራፊክ አደጋን በመቀነስ፣ በሥራ ዕድል፣ ለማህበረሰቡ አማራጭ የመዝናኛ ስፍራ በመፍጠር ነዋሪዎችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው።

የኮሪደር ልማት እየተከናወነባቸው ካሉ ከተሞች አንዷ በሆነችው ሚዛን አማንም ልማቱ በተለያዩ ምዕራፎች ተከፋፍሎ እየተተገበረ ይገኛል።

በአሁኑ ወቅትም በከተማዋ ሁለተኛው ምዕራፍ የሆነውና 4 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የኮሪደር ልማት ግንባታ በመፋጠን ላይ ነው።


የግንባታ ሥራው በቀጣይ አንድ ወር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት እንደሚሆን የተገለጸ ሲሆን የከተማዋን ውበትና ገጽታ ይበልጥ ከማሻሻል ባለፈ ለኑሮ ምቹ እንደሚያደርጋትም ተመላክቷል።

የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤት ምክትል ሥራ አስኪያጅና የግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ወንድሙ አለማየሁ፣ የኮሪደር ልማቱ የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ተወዳዳሪና ለኑሮ ምቹ እያደረጋት መሆኑን ተናግረዋል።


ከዚህ ቀደም በኮሪደር ልማት የቆሻሻ መጣያ የነበሩና ለኑሮ አመቺ ያልነበሩ አካባቢዎች ጭምር ከመልማታቸው ባለፈ መንገዶች እግረኛና ተሽከርካሪን ታሳቢ በማድረግ ሰፍተው በመሰራታቸው ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ እየተፋጠነ መሆኑን ገልጸዋል።

ልማቱ ተጠናክሮ መቀጠሉን የገለጹት አቶ ወንድሙ፣ በአሁኑ ወቅት የከተማዋን ውበትና ገጽታ ይበልጥ የሚያሻሽልና ከ4 ኪሎ ሜትር በላይ የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ግንባታ በሁለተኛ ምዕራፍ እየተፋጠነ መሆኑን አስታውቀዋል።


ልማቱ አረንጓዴ መናፈሻ፣ የእግረኛና የሳይክል መንገድ እንዲሁም ዘመናዊ የመንገድ ዳር መብራትን በማካተት እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመው፣ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልጸዋል።

ማኅበረሰቡ ለልማቱ እያደረገ ያለው ትብብር ከፍተኛ ነው ያሉት አቶ ወንድሙ፣ ለዚህም በአሁኑ ወቅት ከሚከናወነው 4 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት 1 ነጥበ 6 ኪሎ ሜትሩ በማኅበረሰቡ ሙሉ ተሳትፎ የሚሠራ ነው ብለዋል።

የከተማዋ ነዋሪ አቶ ዓለሙ ባቹብ በበኩላቸው እንዳሉት የኮሪደር ልማት ሥራው የሚዛን አማን ከተማን ውበት ከማጉላት ባሻገር በከተማዋ ይስተዋል የነበረን የእግረኛ መንገድ ጥበት ችግር እየፈታ ነው።


ከመጀመሪያ ዙር የኮሪደር ልማት ሥራ ማህበረሰቡ በተለያየ መንገድ ተጠቃሚ መሆኑን ገልጸው፣ አሁን በግንባታ ሂደት ላይ ላለው የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ስኬታማነት የበኩላቸውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026