🔇Unmute
ሰመራ፣ጥቅምት 28/2018(ኢዜአ) ፡- በአፋር ክልል ሰመራ ሎጊያ ከተማ የሚካሄደውን የከተሞች ፎረም ማስተናገድ የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸውን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ።
የኢትዮጵያ የከተሞች ፎረም መካሄድ ከተሞችን እርስበርስ ለማስተዋወቅ፣ በከተሞች መካከል የውድድርና የፉክክር መንፈስ እንዲጎለብት በማድረግ የከተሞችን የልማት ጉዞ ለማፋጠን መነሳሳት እንደሚፈጥር ተመልክቷል።
በተጨማሪም በከተሞች ለቱሪዝም የሚውሉ ታሪካዊ፣ ባህላዊና ማህበራዊ እሴቶች ለማስተዋወቅም ፎረሙ ጉልህ ድርሻ አለው ተብሏል።
ሰመራ ሎጊያ ከተማ “የከተሞች ዕድገት ለኢትዮጵያ ልህቀት" በሚል መሪ ሐሳብ የሚካሄደው 10ኛውን የኢትዮጵያ የከተሞች ፎረም ታስተናግዳለች።
በዚሁ ጉዳይ ላይ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የሰመራ ሎጊያ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አብዱ ሙሳ እንደገለፁት ፎረሙ ሰመራን እና አጠቃላይ በአፋር ክልል ያለውን ተፈጥሯዊና ታሪካዊ ሀብቶችን ለማያስተዋውቅ የሚያግዝ ነው።
ሰመራ ለዝግጅቱ ድምቀት ዘርፈ ብዙ የዝግጅት ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸው በተለይም 6 ሺህ ካሬ ላይ ያረፈ ለዐውደ ርዕይ እና ለሌሎች አገልግሎት የሚውል ስፍራ የዝግጅቱ አንድ አካል መሆኑን ተናግረዋል።
ስፍራው ለዐውደ ርዕይ የሚሆን ሼድ፣ ውሃ፣ መብራት፣ ስልክና የገመድ አልባ ኢንተርኔት እንዲያገኝ ተደርጓል ነው ያሉት።
በዘንድሮው የከተሞች ፎረም ላይ የሚሳተፉ 148 ከተሞች ምርቶቻቸውን የሚያሳዩበት ስፍራም መዘጋጀቱን ገልጸዋል።
ከህዳር 6 እሰከ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ባሉት ተከታታይ ቀናት በተለያዩ ዝግጅቶች እንደሚካሄድ አመልክተው የፎረሙ መክፈቻ እና መዝጊያ ሁነቶች የሚካሄዱበት የሰመራ ስታዲዮም እና ሌሎች ሁነቶች የሚስተናገዱበት የተለያዩ የስብሰባ አዳራሾች መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
ከከተሞች ፎረም ጎን ለጎን በከተማው የተሰሩ የኮሪደር ልማት፣ የልማት ስራዎችና የተፈጥሮ መስህብ መዳረሻ ቦታዎች ጉብኝት እንደሚደረግም ታውቋል።
በፎረሙ ላይ ከዐውደ ርዕይና ሌሎች ሁነቶች በተጨማሪ በተለያዩ መስኮች ጥናታዊ ፅሁፎች እንደሚቀርቡና በከተማ ልማት ፖሊሲ ዙሪያ ውይይት እንደሚደረግ ይጠበቃል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026