የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የከተሞች ፎረምን ማስተናገድ የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተጠናቀዋል

Nov 7, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሰመራ፣ጥቅምት 28/2018(ኢዜአ) ፡- በአፋር ክልል ሰመራ ሎጊያ ከተማ የሚካሄደውን የከተሞች ፎረም ማስተናገድ የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸውን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ።

የኢትዮጵያ የከተሞች ፎረም መካሄድ ከተሞችን እርስበርስ ለማስተዋወቅ፣ በከተሞች መካከል የውድድርና የፉክክር መንፈስ እንዲጎለብት በማድረግ የከተሞችን የልማት ጉዞ ለማፋጠን መነሳሳት እንደሚፈጥር ተመልክቷል።

በተጨማሪም በከተሞች ለቱሪዝም የሚውሉ ታሪካዊ፣ ባህላዊና ማህበራዊ እሴቶች ለማስተዋወቅም ፎረሙ ጉልህ ድርሻ አለው ተብሏል።

ሰመራ ሎጊያ ከተማ “የከተሞች ዕድገት ለኢትዮጵያ ልህቀት" በሚል መሪ ሐሳብ የሚካሄደው 10ኛውን የኢትዮጵያ የከተሞች ፎረም ታስተናግዳለች።

በዚሁ ጉዳይ ላይ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የሰመራ ሎጊያ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አብዱ ሙሳ እንደገለፁት ፎረሙ ሰመራን እና አጠቃላይ በአፋር ክልል ያለውን ተፈጥሯዊና ታሪካዊ ሀብቶችን ለማያስተዋውቅ የሚያግዝ ነው።

ሰመራ ለዝግጅቱ ድምቀት ዘርፈ ብዙ የዝግጅት ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸው በተለይም 6 ሺህ ካሬ ላይ ያረፈ ለዐውደ ርዕይ እና ለሌሎች አገልግሎት የሚውል ስፍራ የዝግጅቱ አንድ አካል መሆኑን ተናግረዋል።

ስፍራው ለዐውደ ርዕይ የሚሆን ሼድ፣ ውሃ፣ መብራት፣ ስልክና የገመድ አልባ ኢንተርኔት እንዲያገኝ ተደርጓል ነው ያሉት።

በዘንድሮው የከተሞች ፎረም ላይ የሚሳተፉ 148 ከተሞች ምርቶቻቸውን የሚያሳዩበት ስፍራም መዘጋጀቱን ገልጸዋል።

ከህዳር 6 እሰከ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ባሉት ተከታታይ ቀናት በተለያዩ ዝግጅቶች እንደሚካሄድ አመልክተው የፎረሙ መክፈቻ እና መዝጊያ ሁነቶች የሚካሄዱበት የሰመራ ስታዲዮም እና ሌሎች ሁነቶች የሚስተናገዱበት የተለያዩ የስብሰባ አዳራሾች መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።

ከከተሞች ፎረም ጎን ለጎን በከተማው የተሰሩ የኮሪደር ልማት፣ የልማት ስራዎችና የተፈጥሮ መስህብ መዳረሻ ቦታዎች ጉብኝት እንደሚደረግም ታውቋል።

በፎረሙ ላይ ከዐውደ ርዕይና ሌሎች ሁነቶች በተጨማሪ በተለያዩ መስኮች ጥናታዊ ፅሁፎች እንደሚቀርቡና በከተማ ልማት ፖሊሲ ዙሪያ ውይይት እንደሚደረግ ይጠበቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.