የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በቂሊንጦ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ባለሀብቶች ኢንቨስት እንዲያደርጉ ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል

Nov 10, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 29/2018 (ኢዜአ)፦በቂሊንጦ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን የአገር ውስጥና የውጭ ባለሀብቶች ኢንቨስት እንዲያደርጉ ምቹ ሁኔታ መኖሩን የልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ቶለሳ በዳዳ ገለጹ።

በቂሊንጦ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ውስጥ ማቲዎስ መባ ኮስሞቲክስ ማኑፋክቸሪንግ የግል ድርጅት የኮስሞቲክስ ፋብሪካ ተመርቋል።


በዚሁ ወቅት የቂሊንጦ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ቶለሳ በዳዳ እንዳሉት፤ የአገር ውስጥም ሆነ የውጪ ባለሀብቶች አስፈላጊ የሆኑ መሰረተ ልማቶች በተሟሉበት በዞኑ በመድሃኒትና በፋርማሲዩቲካል ዘርፎች በስፋት እንዲሰማሩ ጥሪ አቅርበዋል።

አሁን ላይ በልዩ ኢኮኖሚክ ዞኑ ባለሀብቶች በተለያየ የማምረት ደረጃ ላይ እንደሚገኙ ገልጸው፤ አሁንም ተጨማሪ ባለሃብቶች በመምጣት በሚፈልጉት ዘርፍ ተሰማርተው እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።

በልዩ የኢኮኖሚ ዞኑ አሁን ላይ በቋሚና በጊዜያዊነት ለ4 ሺህ 700 በላይ ዜጎች የስራ ዕድል መፈጠሩን ተናግረዋል።

በልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ከውጪ የሚገቡ የመድሃኒትና የፋርማሲዩቲካል ምርቶችን ለመተካት የተለያዩ ኩባንያዎች መድሃኒት እያመረቱ መሆኑን ተናግረዋል።


ማቲዎስ መባ ኮስሞቲክስ ማኑፋክቸሪንግ የግል ድርጅት ባለቤትና ስራ አስፈጻሚ አቶ ማቲዎስ መባ በበኩላቸው፤ ፋብሪካው በመጀመሪያ ዙር በ100 ሚሊዮን ብር ፕሮጀክቱን ማስጀመሩን ገልጸዋል።

ፋብሪካው የኮስሞቲክስ ምርቶችን በአገር ውስጥ በማምረት ከውጪ የሚገባውን ምርት ለመተካት የበኩሉን አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን ገልጸው፤ በሙሉ አቅሙ ወደ ስራ ሲገባ ለ260 ዜጎች ቋሚ የስራ ዕድል እንደሚፈጥር ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026