🔇Unmute
ጎንደር ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦የአጼ ፋሲል አብያተ መንግስት እድሳትና ጥገና ሥራ መንግስት ለታሪካዊ ቅርሶች ጥበቃና ልማት የሰጠውን ልዩ ትኩረት ያሳያል ሲሉ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የቱሪዝምና ማኔጅመንት ትምህርት ክፍል ሃላፊና ተመራማሪ የሺዋስ አቡኔ (ዶ/ር) ተናገሩ።
የሺዋስ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ዘመን ተሸጋሪ ታሪካዊ ቅርሶች የአንድ ሀገርና ህዝብ የማንነት መገለጫዎች ከመሆን ባለፈ የኢኮኖሚ መሰረት ነው።

መንግስት ለዓለም አቀፍ ቅርሱ ትኩረት ሰጥቶ ያከናወነው የእድሳትና ጥገና ሥራ የህዝብና የሀገርን ታሪክ፣ ባህል፣ እሴትና ማንነትን ጠብቆ ለትውልድ ለማሻገር እድል የሚፈጥር ነው ብለዋል።

ዘመን ተሻጋሪ ታሪካዊ ቅርሶች የህዝቦች የአብሮነትና የጋራ ትርክት መገንቢያ አሻራዎች መሆናቸውን ጠቅሰው፤ የጥገና ሥራው ዓለም አቀፍ የቅርስ ጥገና ሳይንስ መስፈርቶችን መሠረት ማድረጉ ዘላቂ እድሜ እንዲኖረው ያደርጋል ሲሉም ገልጸዋል።
የህዝቦችን ታሪክ፣ ባህል፣ እምነት፣ ትውፊት፣ ጥበብና ስልጣኔን አጣምረው የያዙ ታሪካዊ ቅርሶችን ለመጠበቅ፣ ለማልማትና ለትውልድ እንዲሻገሩ ለማድረግ በለውጡ መንግስት የተጀመሩ ተግባራት ፋና ወጊ መሆናቸውንም የሺዋስ (ዶ/ር) አመልክተዋል፡፡
የአጼ ፋሲል አብያተ መንግስቱ ለበርካታ ዓመታት በጥገና እጦት አደጋ ውስጥ የቆየ ዓለም አቀፍ ቅርስ እንደነበር አስታውሰው፤ አሁን መታደሱ መንግስት ለዘመን ተሻጋሪ ቅርሶች ጥበቃና ልማት የሰጠውን ልዩ ትኩረት ያሳያል ሲሉ ተናግረዋል፡፡

እንደ የሺዋስ (ዶ/ር) ገለጻ ጎንደር የበርካታ የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ቅርሶች ባለቤት እንደመሆኗ የአብያተ መንግስቱ ጥገና ተጠናቆ ለጎብኚዎች ክፍት መደረጉ የቱሪስት ፍሰቱን በማሳደግ የቱሪዝም ኢንዱስትሪውን በማነቃቃት በኩል ፋይዳው የጎላ ነው፡፡
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በቅርሶች ደህንነትና ጥበቃ ላይ የጥናትና ምርምር ተግባራትን ሲያከናወን መቆየቱን አስታውሰው፤ በዘርፉ የሰለጠኑ ባለሙያዎችን በማፍራትም ገንቢ ሚና እየተጫወተ ነው ብለዋል፡፡

ዓለም አቀፍ ቅርሱን ከአደጋ ለመጠበቅ መንግስት የወሰዳቸው እርምጃዎች ወሳኝና ወቅታዊ መሆናቸውን ጠቁመው ህዝቡና ባለድርሻ አካላት የቅርሱን ደህንነት በዘላቂነት በመጠበቅ የድርሻቸውን እንዲወጡም አሳስበዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በቅርቡ "የአጼ ፋሲል አብያተ መንግስት አልታደሰም፤ አልተጠገነም ዳግም ተወለደ እንጂ" በማለት የዓለም አቀፍ ቅርሱን ዳግም ትንሳኤ በቦታው ተገኝተው ማብሰራቸው የሚታወስ ነው፡፡
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026