የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የመስህብ ስፍራዎችን በማልማት የቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ እየተሰራ ነው

Nov 21, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሕዳር 12/2018(ኢዜአ)፡-በየም ዞን የሚገኙ ተፈጥሯዊ እና ሰው ሰራሽ የመስህብ ስፍራዎችን በማልማት የቱሪዝም ዘርፍን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ አስታወቀ።

በኢትዮጵያ በርካታ የቱሪስት መዳረሻ ስፍራዎችን በማልማት የቱሪዝም ዘርፍን ለማነቃቃት ባለፉት ዓመታት ሰፊ ስራዎች ተሰርተዋል።


በሀገሪቱ በርካታ የሆኑ ግዙፍ የቱሪዝም ፕሮጀክቶች ግንባታ መጀመሩን እንዲሁም የተጀመሩት መጠናቀቃቸው ሀገሪቱ በዘርፉ ያላትን ዕምቅ አቅም አውጥቶ ለመጠቀም የሚያስችል ነው።

20ኛው የብሔሮች፣ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀንን ምክንያት በማድረግ ከሀገሪቱ ከተለያዩ አካባቢዎች የተውጣጡ የሚዲያ ባለሙያዎች በየም ዞኑ የሚገኙትን የዞፍካር ትክል ድንጋይ፤ የአንገሪ ቤተ-መንግስት፣ የብርብርሳ ፏፏቴ እና የቦር ተራራን ጎብኝተዋል።

የየም ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ሃላፊ መስፍን ሞጋ በዞኑ በርካታ ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ ቅርሶች እንዳሉ ጠቅሰው፤ የመዳረሻ ስፍራዎችን በስፋት በማስተዋወቅ የጎብኝዎች ቁጥር እንዲጨምር ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል።


እነዚህን የቱሪዝም መዳረሻ ሀብቶችን በማልማት የቱሪዝም ዘርፍን ለማነቃቃት በትኩረት እየተሰራ ስለመሆኑ ጠቁመዋል።

የቱሪዝም ዘርፉ ልማት ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይና የሁሉንም ቅንጅታዊ አሰራር የሚፈልግ መሆኑን አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026