🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሕዳር 12/2018(ኢዜአ)፡-በየም ዞን የሚገኙ ተፈጥሯዊ እና ሰው ሰራሽ የመስህብ ስፍራዎችን በማልማት የቱሪዝም ዘርፍን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ አስታወቀ።
በኢትዮጵያ በርካታ የቱሪስት መዳረሻ ስፍራዎችን በማልማት የቱሪዝም ዘርፍን ለማነቃቃት ባለፉት ዓመታት ሰፊ ስራዎች ተሰርተዋል።

በሀገሪቱ በርካታ የሆኑ ግዙፍ የቱሪዝም ፕሮጀክቶች ግንባታ መጀመሩን እንዲሁም የተጀመሩት መጠናቀቃቸው ሀገሪቱ በዘርፉ ያላትን ዕምቅ አቅም አውጥቶ ለመጠቀም የሚያስችል ነው።
20ኛው የብሔሮች፣ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀንን ምክንያት በማድረግ ከሀገሪቱ ከተለያዩ አካባቢዎች የተውጣጡ የሚዲያ ባለሙያዎች በየም ዞኑ የሚገኙትን የዞፍካር ትክል ድንጋይ፤ የአንገሪ ቤተ-መንግስት፣ የብርብርሳ ፏፏቴ እና የቦር ተራራን ጎብኝተዋል።
የየም ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ሃላፊ መስፍን ሞጋ በዞኑ በርካታ ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ ቅርሶች እንዳሉ ጠቅሰው፤ የመዳረሻ ስፍራዎችን በስፋት በማስተዋወቅ የጎብኝዎች ቁጥር እንዲጨምር ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል።

እነዚህን የቱሪዝም መዳረሻ ሀብቶችን በማልማት የቱሪዝም ዘርፍን ለማነቃቃት በትኩረት እየተሰራ ስለመሆኑ ጠቁመዋል።
የቱሪዝም ዘርፉ ልማት ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይና የሁሉንም ቅንጅታዊ አሰራር የሚፈልግ መሆኑን አንስተዋል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026