የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የመስህብ ስፍራዎችን በማልማት የቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ እየተሰራ ነው

Nov 21, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሕዳር 12/2018(ኢዜአ)፡-በየም ዞን የሚገኙ ተፈጥሯዊ እና ሰው ሰራሽ የመስህብ ስፍራዎችን በማልማት የቱሪዝም ዘርፍን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ አስታወቀ።

በኢትዮጵያ በርካታ የቱሪስት መዳረሻ ስፍራዎችን በማልማት የቱሪዝም ዘርፍን ለማነቃቃት ባለፉት ዓመታት ሰፊ ስራዎች ተሰርተዋል።


በሀገሪቱ በርካታ የሆኑ ግዙፍ የቱሪዝም ፕሮጀክቶች ግንባታ መጀመሩን እንዲሁም የተጀመሩት መጠናቀቃቸው ሀገሪቱ በዘርፉ ያላትን ዕምቅ አቅም አውጥቶ ለመጠቀም የሚያስችል ነው።

20ኛው የብሔሮች፣ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀንን ምክንያት በማድረግ ከሀገሪቱ ከተለያዩ አካባቢዎች የተውጣጡ የሚዲያ ባለሙያዎች በየም ዞኑ የሚገኙትን የዞፍካር ትክል ድንጋይ፤ የአንገሪ ቤተ-መንግስት፣ የብርብርሳ ፏፏቴ እና የቦር ተራራን ጎብኝተዋል።

የየም ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ሃላፊ መስፍን ሞጋ በዞኑ በርካታ ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ ቅርሶች እንዳሉ ጠቅሰው፤ የመዳረሻ ስፍራዎችን በስፋት በማስተዋወቅ የጎብኝዎች ቁጥር እንዲጨምር ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል።


እነዚህን የቱሪዝም መዳረሻ ሀብቶችን በማልማት የቱሪዝም ዘርፍን ለማነቃቃት በትኩረት እየተሰራ ስለመሆኑ ጠቁመዋል።

የቱሪዝም ዘርፉ ልማት ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይና የሁሉንም ቅንጅታዊ አሰራር የሚፈልግ መሆኑን አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.