የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

May 28, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን የገለጹት የኢትዮጵያ አየር መንገድ 24ኛ የሀገር ውስጥ መዳረሻ የሆነውን ይህንን ዘመናዊ አውሮፕላን ማረፊያ በዛሬው ዕለት መርቀው ለአገልግሎት ክፍት ባደረጉበት ወቅት ነው።


ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው ላይ በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ በሁሉም አቅጣጫዎች ትላልቅ አውሮፕላኖችን ማስተናገድ የሚችሉ ወደ 30 የሚጠጉ የአየር ማረፊያዎች እንደሚገኙ ጠቁመዋል።

የአየር ማረፊያዎቹ ስርጭት ሀገራዊ አንድነትን እና ልማትን እኩል ለማስፈን ታሳቢ ያደረገ መሆኑን ገልጸው፤በሰሜን 10፣ በምሥራቅ 5፣ በምዕራብ 7 እንዲሁም በደቡብ የሀገሪቱ ክፍል አዲሱን የነገሌ ገዳ አውሮፕላን ማረፊያን ጨምሮ 6 የአየር ማረፊያዎች መኖራቸውን በዝርዝር አብራርተዋል።

የቦረና ሕዝብ የኦሮሞን ማንነት፣ባህልና እሴት ጠብቆ ያቆየ እንዲሁም ከጉጂና ባሌ ማኅበረሰቦች ጋር በትብብር የኖረ ታላቅ ሕዝብ መሆኑን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለሰላም ወዳዱ የቦረና እና ጉጂ ሕዝብ ልማት ብንዘገይም ደርሰንለታል ብለዋል።


አዲሱ የመሠረተ ልማት አውታር አካባቢው ከአዲስ አበባ ካለው የርቀት ስፋት አንጻር የሚፈጥረውን ተግዳሮት በመቅረፍ፤ ለአካባቢው ማኅበረሰብ ዘርፈ-ብዙ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የገነባው ይህ አዲስ አውሮፕላን ማረፊያ እንደ ቦይንግ 737 ማክስ ያሉ ዘመናዊና ግዙፍ አውሮፕላኖችን የማስተናገድ ሙሉ አቅም እንዳለውም ተናግረዋል።

በሳምንት ሦስት የበረራ ቀናትን የሚያስተናግደው ይህ አየር ማረፊያ፤ የክልሎችን ኢኮኖሚያዊ አቅም ከማነቃቃት ባለፈ የድንበር ተሻጋሪ የንግድ ልውውጥንና የቱሪዝም ዘርፍን ለማሳደግ ታላቅ ራዕይ የሰነቀ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አብራርተዋል።

የአየር ማረፊያውን ለገነባው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በቀጣይም ፍትሐዊ ተጠቃሚነትንና የገበያ ትስስርን መሠረት ያደረጉ አዳዲስ የአየር ማረፊያዎች ግንባታ በተለይም በደቡብና ምሥራቅ የሀገሪቱ ክፍሎች ተጠንተው እንደሚቀጥሉም ጠቁመዋል።

ለዚህም ስኬት ሰላም ወዳዱ የጉጂና የቦረና ሕዝብ የጀመረውን የልማት ትብብር አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...

May 28, 2026

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026