🔇Unmute
ሃዋሳ ፤ግንቦት 25/2018 (ኢዜአ)፦በምርጫ ወቅት ያሳዩትን ንቁ ተሳትፎ በልማት ለመድገም መዘጋጀታቸውን የሃዋሳ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ፡፡
በከተማዋ የተለያዩ ምርጫ ጣቢያዎች ጊዜያዊ የምርጫ ውጤት ተለጥፎ ለህዝብ ይፋ የተደረገ ሲሆን ህብረተሰቡም ውጤቶቹን እየተመለከተ ነው።
ጊዜያዊ የምርጫ ውጤቶችን ሲመለከቱ ኢዜአ ያነጋገራቸው የከተማዋ ነዋሪዎች በምርጫ ወቅት ያሳዩትን ንቁ ተሳትፎ በቀጣይ በልማት ሥራ እንደሚደግሙ ተናግረዋል።
ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል በከተማው የለኩ ቀበሌ ነዋሪው አቶ ታከለ ሱንደዶ እና የዳቶ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ቶማስ ፈልታሞ፤ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ በንቃት መሳተፋቸው እንደሚያኮራቸው ገልጸዋል።
አቶ ቶማስ ጨሬ እና አቶ ከበደ ዮናስ በበኩላቸው፤ ህዝብ የስልጣን ባለቤት መሆኑን ባረጋገጠበት ጠቅላላ ምርጫ ያሳዩትን ተሳትፎ በልማት እንደሚደግሙ አረጋግጠዋል።
በሃዋሳ ምርጫ ክልል በ08 ምርጫ ጣቢያዎች ትናንት ድምጽ የተሰጠ ሲሆን የድምጽ ቆጠራ ተጠናቆ የተለጠፉ ጊዜያዊ ውጤቶችን ህዝቡ እየተመለከተ ነው፡፡
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...
Apr 14, 2026
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026