🔇Unmute
ሃዋሳ ፤ግንቦት 25/2018 (ኢዜአ)፦በምርጫ ወቅት ያሳዩትን ንቁ ተሳትፎ በልማት ለመድገም መዘጋጀታቸውን የሃዋሳ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ፡፡
በከተማዋ የተለያዩ ምርጫ ጣቢያዎች ጊዜያዊ የምርጫ ውጤት ተለጥፎ ለህዝብ ይፋ የተደረገ ሲሆን ህብረተሰቡም ውጤቶቹን እየተመለከተ ነው።
ጊዜያዊ የምርጫ ውጤቶችን ሲመለከቱ ኢዜአ ያነጋገራቸው የከተማዋ ነዋሪዎች በምርጫ ወቅት ያሳዩትን ንቁ ተሳትፎ በቀጣይ በልማት ሥራ እንደሚደግሙ ተናግረዋል።
ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል በከተማው የለኩ ቀበሌ ነዋሪው አቶ ታከለ ሱንደዶ እና የዳቶ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ቶማስ ፈልታሞ፤ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ በንቃት መሳተፋቸው እንደሚያኮራቸው ገልጸዋል።
አቶ ቶማስ ጨሬ እና አቶ ከበደ ዮናስ በበኩላቸው፤ ህዝብ የስልጣን ባለቤት መሆኑን ባረጋገጠበት ጠቅላላ ምርጫ ያሳዩትን ተሳትፎ በልማት እንደሚደግሙ አረጋግጠዋል።
በሃዋሳ ምርጫ ክልል በ08 ምርጫ ጣቢያዎች ትናንት ድምጽ የተሰጠ ሲሆን የድምጽ ቆጠራ ተጠናቆ የተለጠፉ ጊዜያዊ ውጤቶችን ህዝቡ እየተመለከተ ነው፡፡
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026