የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

አነስተኛ እና መለስተኛ የመስኖ ፕሮጀክቶች የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት በተጨባጭ እየቀነሱ ነው

Jun 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

መቱ፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የተገነቡ አነስተኛና መለስተኛ የመስኖ ፕሮጀክቶች፣ በአርብቶ አደር አካባቢዎች የሚያጋጥመውን የውሃ እጥረትና ድርቅ ለመቋቋም የሚያስችል አቅም እየፈጠሩ መሆኑን የክልሉ የመስኖና አርብቶ አደሮች ልማት ቢሮ ገለጸ።


የቢሮው ኃላፊ ኢንጂነር ግርማ ረጋሳ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ በውሃ እጥረት ምክንያት በሰዎችና በእንስሳት ላይ የሚደርሰውን የድርቅ ጉዳት ለመቋቋም 'ፊና' የተሰኘ ፕሮጀክት እየተተገበረ ይገኛል።

በፕሮጀክቱ አማካኝነት 73 አነስተኛ እና መለስተኛ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰው ከእነዚህም ውስጥ የ40ዎቹ ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት በቅተዋል ብለዋል።

በአርብቶ አደሩ ማህበረሰብ ዘንድ እየተተገበሩ ያሉት እነዚህ የ“ፊና” ፕሮጀክቶች፣ የድርቅ አደጋን የመቋቋም አቅምን በመገንባት ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከቱ መሆኑን ኃላፊው ጠቁመዋል።

በተለይም በቦረና፣ በሐረርጌና በባሌ ዞኖች በአርብቶ አደር አካባቢዎች በድርቅ ምክንያት በሰዎችና በእንስሳት ላይ ይከሰት የነበረውን ችግር ለመቅረፍ ፕሮጀክቶቹ ከፍተኛ እገዛ ማድረጋቸውን በማሳያነት ጠቅሰዋል።

ፕሮጀክቶቹ የአካባቢውን ማህበረሰብ ከድርቅ ተጋላጭነት በከፍተኛ ሁኔታ እየታደጉ መሆኑንም አንስተው በቀጣይም ልምዱን ሌሎች የውሃ እጥረት ወደሚያጋጥማቸው አካባቢዎች በማስፋፋት፣ ሊከሰት የሚችለውን ችግር አስቀድሞ ለመከላከልና ለመቋቋም በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።

እነዚህ የመስኖ ፕሮጀክቶች ሙሉ በሙሉ ተጠናቅቀው ወደ አገልግሎት ሲገቡ የአካባቢውን የውሃ እጥረት በዘላቂነት ከመቅረፍ ባለፈ በአርብቶ አደሩ ዘንድ በከብት እርባታ ላይ ብቻ የተደገፈውን ህይወት፣ ከግብርና ልማት ስራዎች ጋር በማስተሳሰር ይበልጥ ተጠቃሚ እንደሚያደርጉም ገልጸዋል ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026