የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የደጃዝማች በላይ ዘለቀ አውሮፕላን ማረፊያ አዲስ ተርሚናል የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም ፍሰቱን ያቀላጥፋል

Aug 10, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር ፤ነሐሴ 1/2018(ኢዜአ)፡- የደጃዝማች በላይ ዘለቀ አውሮፕላን ማረፊያ አዲስ ተርሚናል የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም ፍሰቱን እንደሚያቀላጥፍ በዘርፉ የተሰማሩ ግለሰቦች ገለጹ።

በባህር ዳር ከተማ የደጃዝማች በላይ ዘለቀ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአዲስ የተገነባውን ተርሚናል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መመረቃቸው ይታወሳል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ በባህር ዳር የተገነባው ተርሚናል በኢትዮጵያ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቀጥሎ ግዙፉ ተርሚናል መሆኑን መግለጻቸው አይዘነጋም።

አስተያየት ሰጪዎች እንዳሉት የአውሮፕላን ማረፊያው ተርሚናል በአዲስ መልክ መገንባቱ የከተማዋን የቱሪዝም፣ የኢንቨስትመንትና የንግድ እንቅስቃሴ ለማፋጠን ያስችላል ብለዋል።

የባህር ዳር አስጎብኚዎች ማኅበር ሥራ አስኪያጅ አቶ ማስተዋል ዘለቀ እንደገለጹት፤ የተርሚናሉ ዓለም አቀፍ ደረጃውን ጠብቆ መገንባት የቱሪዝም ዘርፉን ዕድገት የሚያፋጥን ነው።

ባህር ዳር በጣና ሐይቅ የሚገኙ ገዳማትን፣ የጢስ አባይ ፏፏቴንና ሌሎች በውስጧ የሚገኙ የመስህብ ሀብቶችን ለመጎብኘት የሚመጡ እንግዶችን በማስተናገድ የምትታወቅ ከተማ መሆኗን ገልጸዋል።

በተጨማሪም ወደ ጎንደር፣ ላሊበላና ሌሎች የቱሪስት መስህብ ስፍራዎች ለመጓዝ ለሚመጡ የውጭና የሀገር ውስጥ ጎብኚዎች ዋነኛ መተላለፊያ በመሆን እያገለገለች ትገኛለች ብለዋል።

ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ተርሚናል መገንባቱም ወደ ከተማዋ የሚመጡ ቱሪስቶችን ምቾትና ደህንነት በመጠበቅ የሀገራችንን ገጽታ ለመገንባት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።

ሌላው በአስጎብኚነት ሥራ የተሰማሩት አቶ አበበ ያረጋል በበኩላቸው፤ ግዙፍና ዘመናዊ ተደርጎ የተገነባው ተርሚናሉ፤ ወደ አካባቢው የሚመጡ ቱሪስቶችን ያለምንም መጨናነቅና እንግልት ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችላል ብለዋል።

ይህም በዘርፉ የሚሰማሩ ባለሀብቶችን በስፋት በመሳብ ከተማዋን ይበልጥ ለማዘመን እንደሚያግዝም አስረድተዋል።

ተርሚናሉ ደረጃውን ጠብቆ መገንባቱ ለጎብኚዎች ፈጣን አገልግሎት በመስጠት የከተማዋን የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ፍሰቱን ያቀላጥፋል ያሉት ደግሞ የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ጋሻው እንዳለው ናቸው።


የተፈጥሮ፣ ሰው ሰራሽና ታሪካዊ ቅርሶች ባለቤት የሆነችውን የባህርዳር ከተማ በኮሪደርና በአረንጓዴ ልማት፣ በሰፋፊ የአስፋልት መንገዶችና በአዲሱ የአባይ ድልድይ ግንባታ በማጀብ ተመራጭ መዳረሻ እንድትሆን መደረጉን አመልክተዋል።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው አዲሱ ተርሚናል መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት ማሳያ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው፤ በቀጣይም ዘመናዊ ሎጆችና ደረጃቸውን የጠበቁ ሆቴሎች ግንባታ ላይ ማተኮር ይገባል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ፓርኩን በማልማትና በመጠበቅ ዘላቂ የገቢ ምንጭ ለማድረግ ቅንጅታዊ ሥራን ማጠናከር ይገባል 

ሮቤ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክን በማልማትና በመጠበቅ ዘላቂ የገቢ ምንጭ ለማድረግ በቅንጅት መሥራት እንደሚገባ የኢትዮጵያ ዱር...

Aug 7, 2026

በዞኑ የመኸር አዝመራን ውጤታማ  ለማድረግ ለኩታ ገጠም እርሻና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩረት ተሰጥቷል

ወልቂጤ ፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በጉራጌ ዞን የመኸር አዝመራን ውጤታማ ለማድረግ ለሰብል እንክብካቤ፣ ለኩታገጠም እርሻና ለግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩ...

Jul 23, 2026

የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያልቁ ተግባራት ይጠናከራሉ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያጎሉ ተግባራት...

Jul 22, 2026

በድሬደዋ ከ71 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወሰዱ

ድሬደዋ፣ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦በድሬደዋ አስተዳደር በበጀት አመቱ ከ71 ቢሊዮን ብር በላይ ያስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መውሰዳቸውን የአስተ...

Jul 21, 2026