የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በአማራ ክልል ከዘንድሮ ዓመት የበልግ ሰብል ልማት ከሶስት ነጥብ አንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ተሰበሰበ

Aug 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል በበልግ ወቅት ከለማው ሰብል ከሶስት ነጥብ አንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው የሰብል ልማት ባለሙያ ወይዘሮ እንዬ አሰፋ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ በመኸር፣ በመስኖና በበልግ ልማት የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትና ከማረጋገጥ ባለፈ ለገበያ የሚተርፍ ምርት ለማምረት እየተቻለ ነው።

በበጋው ወቅትም የበልግ አብቃይ በሆኑ ዞኖች 247 ሺህ 367 ሄክታር መሬት በማልማት ከሶስት ነጥብ አንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰብ መቻሉን ገልጸዋል።

የተገኘው ምርትም የገብስ፣ ስንዴ፣ አኩሪ አተር፣ ቦሎቄ፣ ጤፍ፣ ማሾና ሌሎች ሰብሎች መሆኑን ጠቁመው፤ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የሁለት ሚሊዮን ኩንታል ብልጫ አለው ብለዋል።

ይህም አርሶ አደሩ የምግብ ዋስትናውን እያረጋገጠ እንዲመጣ ከማድረግ ባለፈ፤ ለኢንዱስትሪ ግብአትና ለወጭ ንግድ የሚሆን ምርት በማምረት ተጠቃሚ እንዲሆን እያስቻለ መሆኑን ተናግረዋል።

በደቡብ ወሎ ዞን የተሁለደሬ ወረዳ አርሶ አደር ኢብራሂም አህመድ በሰጡት አስተያየት፤ በዘንድሮው የበልግ ዝናብ አንድ ሄክታር ተኩል ማሳቸውን ቦሎቄና ሽምብራ በመዝራት የተሻለ ምርት ማግኘታቸውን ገልጸዋል።

ይህም በምግብ ራሴን እንድችል ከማድረግ ባለፈ ከምግብ ፍጆታ የተረፈውን ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ እንድሆን አስችሎኛል ብለዋል።

የበልግ ዝናብ ስርጭቱ የተሻለ በመሆኑ በግማሽ ሄክታር መሬት ካለሙት የገብስ ሰብል 15 ኩንታል ምርት ማግኘታቸውን የገለጹት ደግሞ በሰሜን ሸዋ ዞን የጣርማ በር ወረዳ አርሶ አደር አሰፋ መኮነን ናቸው።

በ2017 በጀት ዓመት በክልሉ በበልግ ሰብል ከለማው ከ146 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ከአንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱን ከቢሮው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ፓርኩን በማልማትና በመጠበቅ ዘላቂ የገቢ ምንጭ ለማድረግ ቅንጅታዊ ሥራን ማጠናከር ይገባል 

ሮቤ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክን በማልማትና በመጠበቅ ዘላቂ የገቢ ምንጭ ለማድረግ በቅንጅት መሥራት እንደሚገባ የኢትዮጵያ ዱር...

Aug 7, 2026

በዞኑ የመኸር አዝመራን ውጤታማ  ለማድረግ ለኩታ ገጠም እርሻና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩረት ተሰጥቷል

ወልቂጤ ፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በጉራጌ ዞን የመኸር አዝመራን ውጤታማ ለማድረግ ለሰብል እንክብካቤ፣ ለኩታገጠም እርሻና ለግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩ...

Jul 23, 2026

የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያልቁ ተግባራት ይጠናከራሉ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያጎሉ ተግባራት...

Jul 22, 2026

በድሬደዋ ከ71 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወሰዱ

ድሬደዋ፣ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦በድሬደዋ አስተዳደር በበጀት አመቱ ከ71 ቢሊዮን ብር በላይ ያስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መውሰዳቸውን የአስተ...

Jul 21, 2026