የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የኦዲት ጥራትን ለማሻሻል ባለሙያዎች ዓለም አቀፍ ደረጃዎችን ታሳቢ በማድረግ በቁርጠኝነት ሊሰሩ ይገባል

Aug 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፦የኦዲት ጥራትን ለማሻሻል ባለሙያዎች ዓለም አቀፍ ደረጃዎችን ታሳቢ በማድረግ በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሂሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድ ገለጸ።

የኢትዮጵያ ሒሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድ በኦዲት ጥራት የግምገማ ውጤቶች ዙሪያ ከኦዲት ባለሙያዎችና ባለድርሻ ተቋማት ጋር ተወያይቷል።


የቦርዱ ዋና ዳይሬክተር ውብእሸት ታደለ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ኦዲተሮች የሒሳብና የኦዲት ሪፖርቶችን ጥራት ለማረጋገጥ ዓለም አቀፍ የሙያ ደረጃዎችንና የሥነ-ምግባር መርሆዎችን በጥብቅ ክትትል ነጻና ገለልተኛነት ሆነው ሊሰሩ ይገባል።

በግምገማው የታዩ የኦዲት ጥራት ክፍተቶችን ለመሙላት የባለሙያዎችን አቅም ማጎልበት፣ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ማስፋፋትና የሙያ ደረጃዎችን ማስጠበቅ አስፈላጊ መሆኑም አስገንዝበዋል።

የቦርዱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፍቃዱ አጎናፍር በበኩላቸው፤ ጥራት ያለው የኦዲት ሪፖርት ኢንቨስትመንትን ለመሳብ፣ የታክስ ሥርዓቱን በብቃት ለማስኬድና የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ለማጠናከር ወሳኝ ሚና እንዳለው ጠቁመዋል።


ኢትዮጵያ ወደ ካፒታል ገበያ እየተሸጋገረች በመሆኑም ዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቀ የኦዲት ሥርዓት እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም ኦዲተሮች ለሒሳብ አያያዝና ኦዲት ሪፖርቶች ጥራት መጠበቅ በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፈዋል።


የውጭ ኦዲተሮች ማኅበር ፕሬዝዳንት ዳንኤል ጌታነህ፤ የኦዲት ድርጅቶች የሰው ኃይልና የቴክኖሎጂ አቅማቸውን መፈተሽና ክፍተት ያለባቸውን ማጠናከር የኦዲት ጥራትን ለማሻሻል ቁልፍ ነው ብለዋል።

የኮከብና መልካሙ ኦዲት አድራጊ ድርጅት ተወካይ ኮከብ ሞገስ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ የአካውንቲንግ ትምህርት ከንድፈ ሀሳብ ባሻገር የተግባር ልምምድን ያካተተ እንዲሆን በማድረግ ብቁ የሒሳብና የኦዲት ባለሙያዎችን ማፍራት እንደሚገባ ጠቁመዋል።


ውይይቱም በኦዲት ጥራት የታዩ ክፍተቶችን በመለየት የጋራ መፍትሔ ለማስቀመጥ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ፓርኩን በማልማትና በመጠበቅ ዘላቂ የገቢ ምንጭ ለማድረግ ቅንጅታዊ ሥራን ማጠናከር ይገባል 

ሮቤ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክን በማልማትና በመጠበቅ ዘላቂ የገቢ ምንጭ ለማድረግ በቅንጅት መሥራት እንደሚገባ የኢትዮጵያ ዱር...

Aug 7, 2026

በዞኑ የመኸር አዝመራን ውጤታማ  ለማድረግ ለኩታ ገጠም እርሻና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩረት ተሰጥቷል

ወልቂጤ ፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በጉራጌ ዞን የመኸር አዝመራን ውጤታማ ለማድረግ ለሰብል እንክብካቤ፣ ለኩታገጠም እርሻና ለግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩ...

Jul 23, 2026

የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያልቁ ተግባራት ይጠናከራሉ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያጎሉ ተግባራት...

Jul 22, 2026

በድሬደዋ ከ71 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወሰዱ

ድሬደዋ፣ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦በድሬደዋ አስተዳደር በበጀት አመቱ ከ71 ቢሊዮን ብር በላይ ያስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መውሰዳቸውን የአስተ...

Jul 21, 2026