🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ አስተማማኝ የሳይበር ደህንነት ምህዳር ለመገንባት ወሳኝ የሆነውን ብቁ የሰው ሃይል የማፍራት ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሂሚድ ገለጹ።
5ተኛው ዙር ብሄራዊ የሳይበር ታለንት ሰመር ካምፕ የታዳጊዎች የስልጠና መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ መካሄድ ጀምሯል።

መርሃ ግብሩ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የሚያዘጋጀው ሲሆን በሳይበር ደህንነትና ቴክኖሎጂ ዘርፎች ዝንባሌ ያላቸውን ታዳጊዎችና ወጣቶች ለማፍራት ያለመ ነው።
የሳይበር ደህንነት፣ሶፍትዌር ልማት፣ኮዲንግ፣ አቪዬሽን፣የኤሮስፔስ ቴክኖሎጂ እና ሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘርፎች በመርሃ ግብሩ ተካተዋል።
የሀርድ ዌር እና ሴኪዩሪቲ ዲዛይኖችን ማዘጋጀት የስልጠና መርሀ ግብር ሌላው የትኩረት ማዕከል ነው።
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሃሚድ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤የኢትዮጵያን ዲጂታል ሽግግር ውጤታማ ለማድረግ የሳይበር ደህንነትን ማረጋገጥ ወሳኝ ነው።
ለዚህ ደግሞ በቁ የሰው ሃይል አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመው፤አስተዳደሩ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የሰው ሃይል የማፍራቱን ተግባር አጠናክሮ መቀጠሉን ገልፀዋል።
የሰመር ካምፕ የስልጠና መርሃ ግብር የዚሁ አካል መሆኑን ጠቁመው፤ መርሃ ግብሩ የነገ የኢትዮጵያ ተስፋ የሆኑ ተተኪ ትውልድ በማፍራት ረገድ ትልቅ ድርሻ ያለው መሆኑን ተናግረዋል።
የስልጠና መርሃ ግብሩ በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩንቨርስቲ መጀመሩን አስታውሰው ፤ በአሁኑ ወቅት ስልጠናው በባህር ዳር፣ጅማ ፣ወላይታ ሶዶ፣ሀረማያ ዩንቨርስቲዎችን ጨምሮ በአስተዳደሩ ግቢ ውስጥ እየተሰጠ መሆኑን ጠቁመዋል።

የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አስራት አጸደወይን (ዶ/ር) በበኩላቸው፤የኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብልፅግናን እውን ለማድረግ የቴክኖሎጂ አቅሙ የተገነባ ሀገር ተረካቢ ትውልድ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህ ረገድ ኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የጀመረው ተተኪ ትውልድ የማፍራት ስራ የሚያስመሰግን ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ ለመርሃ ግብሩ ስኬት ዩንቨርሲቲው የሚጠበቅበትን ድርሻ እንደሚወጣ አረጋግጠዋል።
ሰልጣኞችም ኢትዮጵያን የማገልገል አደራ አለባቸሁ፤ለዚህ ደግሞ ስልጠናውን በአግባቡ ተከታትላችሁ ተገቢውን ክህሎት ልትጨብጡ ይገባል ብለዋል።
ሮቤ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክን በማልማትና በመጠበቅ ዘላቂ የገቢ ምንጭ ለማድረግ በቅንጅት መሥራት እንደሚገባ የኢትዮጵያ ዱር...
Aug 7, 2026
ወልቂጤ ፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በጉራጌ ዞን የመኸር አዝመራን ውጤታማ ለማድረግ ለሰብል እንክብካቤ፣ ለኩታገጠም እርሻና ለግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩ...
Jul 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያጎሉ ተግባራት...
Jul 22, 2026
ድሬደዋ፣ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦በድሬደዋ አስተዳደር በበጀት አመቱ ከ71 ቢሊዮን ብር በላይ ያስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መውሰዳቸውን የአስተ...
Jul 21, 2026