የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በሰሜን ሸዋ ዞን በማዕድን ሀብት ልማት አበረታች ውጤት እየተመዘገበ ነው

Aug 14, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደብረ ብርሃን፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሰሜን ሸዋ ዞን የማዕድን ሀብትን አልምቶ ጥቅም ላይ በማዋል አበረታች ውጤት እየተመዘገበ መምጣቱን የዞኑ የማዕድን ሀብት ልማት መምሪያ ገለጸ።

የመምሪያው ኃላፊ አቶ ታደሰ በቀለ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንዳሉት፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የባህላዊ ማዕድናት ምርትና ግብይት ሕጋዊ መስመር ተከትሎ እንዲከናወን ተደርጓል።

በዚህም 7 ነጥብ 7 ሚሊዮን ቶን ምርት ለሀገር ውስጥ ገበያ ማቅረብ እንደተቻለ ነው ያመለከቱት።

የኢንዱስትሪ፣ የኮንስትራክሽንና የከበሩ ማዕድናት በጥራት ተመርተው ለገበያ ማቅረብ በመቻሉም ከ4 ነጥብ 4 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ማዳን እንደተቻለ ገልጸዋል።

ከዚህም ባለፈ በአካባቢው ጂፕሰም፣ ላይምስቶንና ኦፓልን ጨምሮ ከ27 በላይ የከበሩና የኢንዱስትሪ ማዕድናት መኖራቸውን ጥናት ማረጋገጥ መቻሉን ተናግረዋል።

በቀጣይም ዘርፉን በዘመናዊ መንገድ ለመምራትና የግብይት እሴትን ለማጠናከር በጣርማበር ወረዳ የከበሩ ማዕድናት መግዣና መሸጫ የገበያ ማዕከል እየተገነባ ይገኛል ብለዋል።

የአካባቢውን ማህበረሰብ በኢኮኖሚ ተጠቃሚ ለማድረግና የስራ ዕድል ለመፍጠር በግል እና በኢንተርፕራይዝ ለተደራጁ 247 ባህላዊ ማዕድን አምራች ማህበራት የስራ ፈቃድ መሰጠቱንም አክለው ገልጸዋል።

በእንሳሮ ወረዳ የ"ሽመልስ ማሞ እና ጓደኞቻቸው" ህብረት ሽርክና ማህበር ሰብሳቢ አቶ ሽመልስ ማሞ በበኩላቸው፤ ማህበሩ ለግንባታ አገልግሎት የሚውል ማዕድን አምርቶ ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆኑን ተናግረዋል።

ማህበሩ 47 አባላት ያሉት ሲሆን፣ የማዕድን ሀብቱን አምርቶ ከሚገኘው ሽያጭ አባላቱን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል።

በመርሐቤቴ ወረዳ ቁም አምባ ቀበሌ “ሲልካ“ የተባለ ለጠርሙስ ምርት በግብዓትነት የሚያገለግል ማዕድን እሴት ጨምረው በማቅረብ ተጠቃሚ እንደሆኑ የገለጹት ደግሞ የ"ማክን ትሬዲንግ" ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ ሙሉጌታ ደምሴ ናቸው።

ድርጅታቸው አሁን ላይ ከ100 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል መፍጠሩን ጠቅሰው፤ በቀጣይም ምርታቸውን በተሻለ ፍጥነትና ጥራት ለገበያ ለማቅረብ እየሰሩ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሀብቶች ወደ ሥራ ገብተዋል

ሚዛን አማን፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በ2018 በጀት ዓመት ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሀብቶች ፈቃድ...

Aug 14, 2026

ፓርኩን በማልማትና በመጠበቅ ዘላቂ የገቢ ምንጭ ለማድረግ ቅንጅታዊ ሥራን ማጠናከር ይገባል 

ሮቤ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክን በማልማትና በመጠበቅ ዘላቂ የገቢ ምንጭ ለማድረግ በቅንጅት መሥራት እንደሚገባ የኢትዮጵያ ዱር...

Aug 7, 2026

በዞኑ የመኸር አዝመራን ውጤታማ  ለማድረግ ለኩታ ገጠም እርሻና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩረት ተሰጥቷል

ወልቂጤ ፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በጉራጌ ዞን የመኸር አዝመራን ውጤታማ ለማድረግ ለሰብል እንክብካቤ፣ ለኩታገጠም እርሻና ለግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩ...

Jul 23, 2026

የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያልቁ ተግባራት ይጠናከራሉ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያጎሉ ተግባራት...

Jul 22, 2026