🔇Unmute
ጂንካ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከእንስሳት ሀብት የሚገኘውን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለማሳደግ ለእንስሳት ጤና ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ፡፡
በክልሉ ዲመካ ከተማ ከ446 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ለሚገነባው የዲመካ ክልላዊ የእንስሳት ጤና ላቦራቶሪ ዛሬ የመሰረት ድንጋይ ተቀምጧል።
የመሰረት ድንጋዩን ያስቀመጡት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ በክልሉ ከእንስሳት ሀብት የሚገኘውን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለማሳደግ ለእንስሳት ጤና ትኩረት ተሰጥቷል፡፡

በክልሉ የእንስሳት እርባታ በተለይ የአርብቶ አደሩ የኑሮ መሰረት በመሆኑ የእንስሳትን ጤና መጠበቅ የአርብቶ አደሩን ሕልውና መጠበቅ መሆኑን ተናግረዋል።
ዲመካ ላይ የሚገነባው የእንስሳት ጤናላቦራቶሪ ከአካባቢው አልፎ ለክልሉም ጥቅም የሚሰጥና ለእንስሳት ጤና መጠበቅ ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው አመልክተዋል።
የላቦራቶሪ ፕሮጀክቱ ግንባታ በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል ይደረጋል ብለዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መስኖና ቆላማ አካባቢ ልማት ቢሮ የአርብቶ አደር አደጋ ሥጋት ቅነሳና አካታች የኢኮኖሚ እሴት ማሻሻያ ፕሮጀክት አስተባባሪ ዶክተር ስዩም መታፈሪያ በበኩላቸው እንዳሉት፤ የዲመካ ክልላዊ የእንስሳት ጤና ላቦራቶሪ ድንበር ዘለል የእንስሳት በሽታዎችን ለመከላከልና አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ነው።

ለግንባታው ከ446 ሚሊዮን ብር በላይ መመደቡን ጠቅሰው፣ ላቦራቶሪው በመንግሥት እና በዓለም ባንክ ድጋፍ እንደሚገነባ አስታውቀዋል።
ግንባታውን በአንድ ዓመት ከ6 ወር ጊዜ ለማጠናቀቅ መታቀዱን ገልጸው፣ ላቦራቶሪው የእንስሳት በሽታ ምልክቶች ሲኖሩ አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት ያስችላል ብለዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ከዚህ ቀደም በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ወዳሉ ሀገር አቀፍ የእንስሳት ጤና ላቦራቶሪዎች ናሙና በመላክ ሲባክን የነበረውን ጊዜና ገንዘብ ለመቆጠብ ያስችላል ብለዋል።
ሚዛን አማን፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በ2018 በጀት ዓመት ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሀብቶች ፈቃድ...
Aug 14, 2026
ሮቤ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክን በማልማትና በመጠበቅ ዘላቂ የገቢ ምንጭ ለማድረግ በቅንጅት መሥራት እንደሚገባ የኢትዮጵያ ዱር...
Aug 7, 2026
ወልቂጤ ፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በጉራጌ ዞን የመኸር አዝመራን ውጤታማ ለማድረግ ለሰብል እንክብካቤ፣ ለኩታገጠም እርሻና ለግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩ...
Jul 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያጎሉ ተግባራት...
Jul 22, 2026