የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ወጣቶችን በክህሎትና በአመለካከት ብቁ በማድረግ በሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ለውጥ ማምጣት ተችሏል

Aug 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሐዋሳ፤ ‎ነሐሴ 8/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል ወጣቶችን በክህሎትና በአመለካከት ብቁ በማድረግ በሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ትርጉም ያለው ለውጥ ማምጣት መቻሉን የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ አስታወቀ፡፡

በኢትዮጵያ ኢንተርፕርነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት ለወጣቶች ቀጣይነት ያለው የሥራ ዕድል ፈጠራ ፕሮግራም ''SEED'' በሲዳማ ክልል የሦስት ዓመት የሥራ አፈጻጸምና ቀጣይ አቅጣጫ ላይ የሚመክር መድረክ በሐዋሳ ከተማ ተካሄዷል፡፡


የሲዳማ ክልል ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሀገረጽዮን አበበ በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ በክልሉ ወጣቶችን በክህሎትና በአመለካከት በማብቃት በሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ትርጉም ያለው ለውጥ ማምጣት ተችሏል፡፡

ከዚህ ቀደም የነበረው የሥራ ዕድል ፈጠራ ክህሎት መር ባለመሆኑ የተነሳ የሥራ ዕድል የተፈጠረላቸው ዜጎች ውጤታማ አለመሆን የዘርፉ ፈተና ሆኖ መቆየቱን አስታውሰዋል።

ዘርፉ በዜጎች ክህሎትና አመለካከት ላይ የተመሠረተ እንዲሆን እንደ ሀገር አቅጣጫ ተይዞ መሥራት ከተጀመረ በኋላ፤ በተለይ ወጣቶች በተሻለ አቅምና ፍላጎት ወደ ሥራ እንዲገቡ መደረጉን ጠቁመዋል፡፡


በዚህም ውጤታማ የሆኑና ከራሳቸው አልፈው ለሌሎች የሥራ ዕድል መፍጠር የቻሉ በርካታ ወጣቶችን ማፍራት እንደተቻለ ጠቅሰው፤ በዚህ ረገድ የባለድርሻ አካላት ቅንጅት ከፍተኛ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

የቢሮው ምክትልና የሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ከፍያለው ከበደ በበኩላቸው፤ አጋር አካላትን ከሥልጠና ተቋማት ጋር በማቀናጀት የክህሎት ክፍተቶችን የመሙላት እና ወደ ሥራ የሚገቡትን የማብቃት ሥራ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡


ቅድሚያ ለክህሎትና አመለካከት በመስጠት የፋይናንስ፣ እንዲሁም የመሥሪያና የመሸጫ ቦታዎችን የማቅረብ ሥራ እየተሠራ መሆኑንም አክለዋል፡፡

በኢትዮጵያ ኢንተርፕረነርሺፕ ልማት ኢንስቲቲዩት የሲዳማ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ የደቡብ ኢትዮጵያና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልሎች አስተባባሪ አቶ ጌትነት ሳሙኤል፤ በኢንስቲትዩቱ የሚመራው የሥራ ዕድል ፈጠራ ፕሮግራም በአምስት ዓመታት ውስጥ ለ1 ሚሊዮን ወጣቶች ቀጣይነት ያለው የሥራ ዕድል የመፍጠር ዕቅድ አለው ብለዋል፡፡


ፕሮግራሙ ከተመረጡ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ጋር በመሆን የክህሎት ሥልጠና የመስጠት፣ እንዲሁም ከፋይናንስ ተቋማት ጋር በመቀናጀት የብድር አቅርቦት የማመቻቸት ሥራ እንደሚሠራ አስረድተዋል፡፡

በፕሮግራሙ በሲዳማ ክልል በሦስት ዓመታት ውስጥ ከ27 ሺህ በላይ ወጣቶች የክህሎት ሥልጠና ያገኙ ሲሆን፤ ከእነዚህ ውስጥ ከ19 ሺህ በላይ የሚሆኑት የሥራ ዕድል እንደተፈጠረላቸው አብራርተዋል፡፡

ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በመቀናጀትም ለኢንተርፕራይዞች ከ181 ሚሊዮን ብር በላይ ብድር እንደተሰራጨ ጠቁመዋል፡፡


በፕሮግራሙ ድጋፍ ካገኙ ኢንተርፕራይዞች መካከል የጠይም ጋርመንት አባል የሆነችው ወጣት ቤርሳቤህ አለማየሁ እና የጃዋታ ጨርቃ ጨርቅ ማኅበር አባል የሆነችው ወጣት ራህመት ሁሴን፤ በፕሮግራሙ ባገኙት ሥልጠና ከዚህ ቀደም የነበረባቸውን የሂሳብ አያያዝና ሌሎች ክፍተቶች በመሙላት በሥራቸው ትርፋማ መሆን እንደቻሉ ገልጸዋል፡፡


በመድረኩ የክልል፣ የዞንና የከተማ አስተዳደር የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ተቋማት አመራሮች ተገኝተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሀብቶች ወደ ሥራ ገብተዋል

ሚዛን አማን፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በ2018 በጀት ዓመት ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሀብቶች ፈቃድ...

Aug 14, 2026

ፓርኩን በማልማትና በመጠበቅ ዘላቂ የገቢ ምንጭ ለማድረግ ቅንጅታዊ ሥራን ማጠናከር ይገባል 

ሮቤ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክን በማልማትና በመጠበቅ ዘላቂ የገቢ ምንጭ ለማድረግ በቅንጅት መሥራት እንደሚገባ የኢትዮጵያ ዱር...

Aug 7, 2026

በዞኑ የመኸር አዝመራን ውጤታማ  ለማድረግ ለኩታ ገጠም እርሻና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩረት ተሰጥቷል

ወልቂጤ ፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በጉራጌ ዞን የመኸር አዝመራን ውጤታማ ለማድረግ ለሰብል እንክብካቤ፣ ለኩታገጠም እርሻና ለግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩ...

Jul 23, 2026

የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያልቁ ተግባራት ይጠናከራሉ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያጎሉ ተግባራት...

Jul 22, 2026