የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በአፋር ክልል ገቢን በተቀናጀ መንገድ የመሰብሰብ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል

Aug 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሰመራ፤ ነሐሴ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በአፋር ክልል ገቢን በተቀናጀ መንገድ የመሰብሰብ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የመሬት ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡመር ኑር ተናገሩ።

በክልሉ ያለፈው በጀት ዓመት አፈፃፀምና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ የክልል፣ የዞን፣ የወረዳ እና የከተማ አስተዳደር የሥራ ኀላፊዎች በተገኙበት ውይይት ተካሂዷል።


የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የመሬት ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡመር ኑር እንዳሉት የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ የክልሉን ገቢ በቅንጅት የመሰብሰቡ ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል።

የበጀት ዓመቱን የገቢ ዕቅድ ለማሳካት በሚከናወኑ ቅንጅታዊ ሥራዎች በየደረጃ የሚገኘው አመራር ወሳኝ ሚና እንዳለውም ጠቁመዋል።

ለመሰብሰብ የተያዘውን የገቢ ዕቅድ ለማሳካት የግብር ስወራን በቅንጅት ከመቆጣጠር ባለፈ ህብረተሰቡ ግብሩን በተለያዩ አማራጮች እንዲከፍል ግንዛቤውን የማሳደግ ሥራ እንደሚሰራም አመልክተዋል።

ከዚህ በተጨማሪ የገቢ ዕቅዱን ለማሳካት ባለፈው ዓመት በቅንጅት በተከናወኑ ሥራዎች የተገኘውን ወጤት በመቀመር ይሰራል ሲሉም አክለዋል።

የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ አቶ አወል አብዱ በበኩላቸው እንዳሉት በክልሉ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ ለመሰብሰብ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።

ከዓመት ወደ ዓመት ገቢን የመሰብሰብ አቅም እያደገ መምጣቱን ገልፀው የዘንድሮውን ዓመት በተያዘለት የጊዜ ገደብ ሰብስቦ ለማጠናቀቅ በትጋት ይሰራል ብለዋል።

አመራሩ ለገቢ ዕቅዱ መሳካት በተናበበ መልኩ ከመስራት ባለፈ ለሚያጋጥሙ ችግሮች በጋራ መፍትሄ እየሰጠ መሄድ እንዳለበትም አስገንዝበዋል።

በተለይም ከዚህ ቀደም የሚስተዋሉ ደረሰኝ አለመቁረጥና ሌሎች መሰል ችግሮችን ለማስወገድ ለንግዱ ማህበረሰብ ግንዛቤ እየሰተጠ መሆኑንም አመልክተዋል።

ክልሉ በዘንድሮ በጀት ዓመት ከ16 ቢሊዮን ብር በላይ ለመሰብሰብ አቅዶ ወደ ሥራ መገባቱ የሚታወስ ነው።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሀብቶች ወደ ሥራ ገብተዋል

ሚዛን አማን፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በ2018 በጀት ዓመት ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሀብቶች ፈቃድ...

Aug 14, 2026

ፓርኩን በማልማትና በመጠበቅ ዘላቂ የገቢ ምንጭ ለማድረግ ቅንጅታዊ ሥራን ማጠናከር ይገባል 

ሮቤ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክን በማልማትና በመጠበቅ ዘላቂ የገቢ ምንጭ ለማድረግ በቅንጅት መሥራት እንደሚገባ የኢትዮጵያ ዱር...

Aug 7, 2026

በዞኑ የመኸር አዝመራን ውጤታማ  ለማድረግ ለኩታ ገጠም እርሻና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩረት ተሰጥቷል

ወልቂጤ ፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በጉራጌ ዞን የመኸር አዝመራን ውጤታማ ለማድረግ ለሰብል እንክብካቤ፣ ለኩታገጠም እርሻና ለግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩ...

Jul 23, 2026

የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያልቁ ተግባራት ይጠናከራሉ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያጎሉ ተግባራት...

Jul 22, 2026