የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት እያከናወነች ያለችው ውጤታማ ተግባር ለቀጣናው የዲጂታል ትብብር በተሞክሮነት የሚጠቀስ ነው

Sep 10, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ጳጉሜን 4 /2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ በሳይበርና መረጃ ደህንነት እያከናወነች ያለችው ውጤታማ ተግባር ለቀጣናው የዲጂታል ትብብር በተሞክሮነት የሚጠቀስ መሆኑን የምስራቅ አፍሪካ መንግሥታት በይነ-መንግሥታዊ ባለሥልጣን (ኢጋድ) ገለጸ።

የኢጋድ የኢኮኖሚ ትብብርና ቀጣናዊ ውህደት ዳይሬክተር ሙሂየልዲን አልቶሃሚ ጠሃ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) እና በቴክኖሎጂ ዘርፍ ያካበተችው ተሞክሮ ለኢጋድ አባል ሀገራት የተሻለ ትምህርት የሚሰጥ ነው።

በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ባደረጉት ጉብኝት በሳይበር ደህንነት፣ በዳታ ጥበቃና በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራት ለቀጣናዊ የእውቀት ሽግግር ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳላቸው መገንዘባቸውን ተናግረዋል።

ኢጋድ በአሁኑ ወቅት እያዘጋጀው የሚገኘው የሰው ሰራሽ አስተውሎት ማዕቀፍ የአባል ሀገራትን የዘርፉ ፖሊሲ፣ የመረጃ ጥበቃና የአጠቃቀም ሥነ-ምግባር፣ ተቋማዊ አቅም፣ የሰው ኃይል ልማትና የእውቀት ሽግግር ላይ አተኩሮ እንደሚሠራ አስረድተዋል።

የኢጋድ አባል ሀገራት በዘርፉ ያለባቸውን የአቅም ክፍተት ለመሙላትና ቀጣናዊ ልማትን ለማፋጠን እንደ ኢትዮጵያ የተሻለ አቅም ካላቸውና ውጤታማ ተግባር እያከናወኑ ከሚገኙ ሀገራት ልምድና ተሞክሮ መውሰድ እንዳለባቸው አሳስበዋል።

ሰው ሰራሽ አስተውሎት በቀጣናው በተለይም በግብርና፣ በጤና፣ በትምህርት እንዲሁም በሰላምና ደህንነት ዘርፎች የሚከናወኑ የልማት ተግባራትን ለማገዝ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው አመልክተዋል።

የቴክኖሎጂውን ጥቅም በስፋት ለማጎልበት የሰው ኃይል ልማትን ማጠናከር፣ ቀጣናዊ ትብብርን ማሳደግና የእውቀት ሽግግር ማድረግ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።


የቴክኖሎጂ ባለሙያው ሰለሞን ካሳ በበኩሉ፤ የሰው ሰራሽ አስተውሎት እንደ ጤና እና ግብርና ያሉ ዘርፎችን ለመደገፍ ብሎም እንደ ድርቅ ያሉ ተፈጥሯዊ አደጋዎችን አስቀድሞ በመተንበይ ምርታማነትና ዕድገትን እንደሚያፋጥን ገልጿል።

ኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲቲዩት በማቋቋም፣ ፖሊሲ በመንደፍ እና ምርምሮችን በማካሄድ ለአጎራባች ሀገራት ጭምር አርዓያ የሚሆን ተግባር እያከናወነች መሆኑንም ተናግሯል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026

በሐረሪ ክልል በኢንቨስትመንት ዘርፍ የተፈጠረው ምቹ ሁኔታ ውጤታማ እያደረገን ነው -ባለሀብቶችና ወጣቶች

ሀረር፤ ነሐሴ 20/2018 (ኢዜአ)፡- በሐረሪ ክልል በኢንቨስትመንት ዘርፍ የተፈጠረው ምቹ ሁኔታ ውጤታማ እያደረጋቸው መሆኑን ባለሀብቶችና ወጣቶች ገለጹ። ...

Aug 27, 2026