የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

Aug 31, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት ቢሮ ገለጸ፡፡

በጋምቤላ ክልል የሚገኙት ታላላቅ ወንዞችና የውሃ አካላት ክልሉን በዓሳ ሀብት ከፍተኛ አቅም ካላቸው የኢትዮጵያ አካባቢዎች አንዱ ያደርጉታል።

ክልሉ በዓመት በሺዎች ቶን የሚቆጠር ዓሳ የማምረት አቅም ቢኖረውም፣ ዘርፉ ለብዙ ዓመታት በባህላዊ የአሳ ማጥመድ ዘዴዎችና በግብአት እጥረት ምክንያት የሚገባውን ያህል ጥቅም ሳይሰጥ ቆይቷል።

በክልሉ የሚገኙ አሳ አጥማጆች ዘመናዊ የዓሳ ማጥመጃ መረቦች፣ የጀልባዎችና የበረዶ ሳጥን አቅርቦት እጥረት ስለነበረባቸው፣ እንዲሁም ከምርት በኋላ የሚባክነውን የዓሳ መጠን የመቀነስና የገበያ ትስስር የመፍጠር ክፍተቶች ነበሩባቸው።

ይህን ክፍተት ለመሙላት የጋምቤላ ክልል እንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት ቢሮ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ትኩረት ሰጥቶ ሲሰራ ቆይቷል።


ቢሮው ለአሳ አጥማጆችና ለተደራጁ ማህበራት የቁሳቁስና የግብአት ድጋፍ ከመስጠቱም በላይ፣ በዘመናዊ የዓሳ አመራረት፣ አያያዝ፣ ጥራት አጠባበቅና ጥበቃ ዙሪያ ተከታታይ የሙያና ቴክኒክ ስልጠናዎችን ሲሰጥ ቆይቷል።

የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ክርምስ ሌሮ እንዳረጋገጡት፣ እነዚህ የተደረጉት የግብአት አቅርቦቶችና የሙያ ድጋፎች አሳ አጥማጆቹ አሰራራቸውን ከባህላዊ ወደ ዘመናዊ እንዲያሸጋግሩ፣ የምርት መጠናቸውን እንዲጨምሩ እና የቤተሰቦቻቸውን ገቢ በማሻሻል የአካባቢውን ኢኮኖሚ እንዲያነቃቁ አስችለዋል።

በተለይም የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ተግባራዊ መደረጉ ዘርፉን በእውቀት በመምራት የአስጋሪዎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ማገዙን ገልጸዋል።

በክልሉ የአሳ ልማትን ውጤታማ ለማድረግ በወንዞች፡ በሃይቆችና ሰው ሰራሽ የውሃ አማራጮች ጭምር በመተግበር የዘርፉን ኢኮኖሚያዊ አቅም ማሳደግ ተችሏል ብለዋል።


በዚህም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 5 ሺህ 970 ቶን አሳ ምርት ታቅዶ ከእቅድ በላይ 10 ሺህ 840 ቶን ማምረት መቻሉን ገልጸዋል።

የዓሳ ሃብት ልማቱን ለስራ እድል ፈጠራ ለማዋል በተደረገው ጥረትም በማህበር ለተደራጁ ወጣቶች የዓሳ ማስገሪያ፡ ማቀናባሪያና የማጓጓዣ ግብዓቶች እንዲያገኙ መደረጉንም ተናግረዋል።

በተያዘው በጀት ዓመትም ዘርፉን ይበልጥ ለማሳደግ ከሌማት ቱትሩፋት መርሃግብር ጋር አቀናጅቶ እንደሚሰራም ገልጸዋል።


በአኝዋሃ ዞን በአቦቦ ወረዳ የሪዮ ቤር ዓሳ አምራች ማህበር አባል ወጣት ዳክ ኡጉት፤ የዓሳ ማስገሪያና የትራንስፖርት ድጋፍ በማግኘታቸው የዓሳ ምርታቸውን በጥራትና በወቅቱ ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚነታቸውን ማሳደጋቸውን ተናግሯል።


የዓሳ ምርታማነታቸውን በጥራትና በብዛት ለገበያ በማቅረብ ተወዳዳሪነታቸውን ማሳደግ እንደቻሉ የገለጸው ደግሞ ሌላው የማህበሩ አባል ወጣት ጆክ ኡፑቲ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026

በሐረሪ ክልል በኢንቨስትመንት ዘርፍ የተፈጠረው ምቹ ሁኔታ ውጤታማ እያደረገን ነው -ባለሀብቶችና ወጣቶች

ሀረር፤ ነሐሴ 20/2018 (ኢዜአ)፡- በሐረሪ ክልል በኢንቨስትመንት ዘርፍ የተፈጠረው ምቹ ሁኔታ ውጤታማ እያደረጋቸው መሆኑን ባለሀብቶችና ወጣቶች ገለጹ። ...

Aug 27, 2026

የኢትዮጵያ የማዕድን ምርት እመርታ

በሙሴ መለሰ የኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ በአገር በቀል የኢኮኖሚና የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ታግዞ፣ ባለፉት ዓመታት የታዩበትን የአሰራርና መዋቅራዊ ችግሮች በመ...

Aug 22, 2026

የሌማት ትሩፋት መርሐ ግብር ዘላቂ ተጠቃሚነታችንን ለማረጋገጥ አስችሎናል-አርሶ አደሮች

ደብረብርሃን፤ ነሀሴ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሌማት ትሩፋት መርሐ ግብር በመሳተፍ ዘላቂ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ መቻላቸውን አርሶ አደሮች ገለጹ። የሌማት ት...

Aug 21, 2026