የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የሙዝ ምርት በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪነቱን ለማሳደግ የባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ጥረት ወሳኝ ነው

Aug 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ)፦ የሙዝ ምርትን በዓለም አቀፍ ገበያ ያለውን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ የጥራት ማሻሻያና የባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ጥረት ወሳኝ መሆኑን የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ (ዶ/ር) ገለጹ።

የኢትዮጵያ አበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ አምራች ላኪዎች ማህበር የሙዝ ወጪ ንግድ ላይ ያተኮረ ሀገር አቀፍ ጉባዔ እያካሄደ ይገኛል፡፡


የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሙዝ ምርት መጠን ቢኖርም ለውጭ ንግድ የሚቀርበው ለጎረቤት ሀገራት ብቻ ነው።

ኢትዮጵያ ያላትን ለግብርና የተመቹ አግሮ-ኢኮሎጂያዊ ሁኔታዎች ወደ ሀብትና ካፒታል በመቀየር ዓለም አቀፍ የገበያ መዳረሻዎችን ማስፋት ይገባል ብለዋል።

የመንግሥትና የግሉ ዘርፍ ትብብር በሆርቲካልቸር ዘርፍ ስኬቶች እንዲመዘገቡ ማድረጉን በማንሳት፤ በአትክልትና ፍራፍሬ ያለውን ተቋማዊ ልምድ፣ የሎጂስቲክስ እውቀት እና ዓለም አቀፍ የገበያ ትስስር ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።

የግብርና ሚኒስቴር ዘርፉን ገበያ ተኮር፣ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገርና ዘላቂ ለማድረግ በርካታ የፖሊሲ እና የስትራቴጂ ማዕቀፎችን ቀርጿል ብለዋል።

የኢትዮጵያን ሆርቲካልቸር ዘርፍ ለማሳደግ የ10 ዓመት ብሔራዊ የሆርቲካልቸር ስትራቴጂ በመቅረጽ ለዘርፉ እድገት በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በመሆኑም የሙዝ ምርት ዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ የጥራት ማሻሻያና የባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ጥረት ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።

በአበባና በአትክልት ዘርፍ የተገነባው ተቋማዊ ልምድ፣ የሎጂስቲክስ እውቀት እና ዓለም አቀፍ የገበያ ትስስር ለሙዝ ኢንዱስትሪው ስኬት መጠቀም ይገባልም ብለዋል።


የኢትዮጵያ አበባ አትክልትና ፍራፍሬ አምራች ላኪዎች ማህበር ዋና ዳይሬክተር ቴዎድሮስ ዘውዴ፤ በሆርቲካልቸር ኢንዱስትሪ ዘርፍ ያለውን እምቅ አቅም ለመጠቀም ከግብርና ሚኒስቴር እና ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየሠሩ መሆኑን ገልጸዋል።

በዓለም አቀፍ ደረጃ በብዛት ከሚመረቱ የፍራፍሬ ዝርያዎች አንዱ መሆኑን ገልጸው፤ በኢትዮጵያ ከምግብነት ባለፈ ለበርካታ ዜጎች የገቢ ምንጭና ሥራ ዕድል ፈጥሯል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026

የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ማስፈፀሚያ ከ18 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት አጸደቀ

ጋምቤላ፤ ነሀሴ 12/2018 (ኢዜአ)፡- የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ማስፈፀሚያ ከ18 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት አፀደቀ። ...

Aug 19, 2026

የአርብቶ አደሩን ማሕበረሰብ ህይወት በዘላቂነት ለመለወጥ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ስኬታማ ናቸው

ጂንካ፤ ነሐሴ 12/2018(ኢዜአ) ፡-በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኙ አርብቶ አደሮችን ህይወት በዘላቂነት ለመለወጥ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ስኬታማ መሆናቸውን...

Aug 19, 2026

የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን እያሳደገልን ነው

ጊምቢ፣ ነሐሴ4/2018 (ኢዜአ) ፡-በምዕራብ ወለጋ ዞን እየተተገበረ የሚገኘው የሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብር የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ተጨማሪ የገቢ ም...

Aug 11, 2026