የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የአርብቶ አደሩን ማሕበረሰብ ህይወት በዘላቂነት ለመለወጥ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ስኬታማ ናቸው

Aug 19, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጂንካ፤ ነሐሴ 12/2018(ኢዜአ) ፡-በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኙ አርብቶ አደሮችን ህይወት በዘላቂነት ለመለወጥ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ስኬታማ መሆናቸውን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ፡፡

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የዲላ ክላስተር አስተባባሪና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር)፤ በደቡብ ኦሞ ዞን በና-ፀማይ ወረዳ ወይጦ ክላስተር በአርብቶ አደሮች በኩታ ገጠም የለማውን የሽንኩርት ማሳ ጎብኝተዋል።


ዶክተር መሪሁን በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ አርብቶ አደሩን ማህበረሰብ ከእንስሳት እርባታው በተጨማሪ በእርሻ ስራ በማሰማራት የገቢ ምንጫቸውን ለማሳደግ የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው።

የክልሉ መንግስት የአርብቶ አደሮችን ህይወት በዘላቂነት ለመለወጥ የሚያስችሉ ተግባራት በማከናወን ስኬታማ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ነው የጠቆሙት።

ማሕበረሰቡን ከከብት እርባታው በተጨማሪ በእርሻ ስራ በማሰማራት ወደ ብዝሃ ኢኮኖሚ ዘርፍ የማሸጋገር ስራ በትኩረት በመሰራቱ ውጤቱ መመዝገቡን ነው የተናገሩት።

ለዚህም በኩታ ገጠም እርሻ የተሰማሩ አርብቶ አደሮች ማሳያ ናቸው ያሉት ዶክተር መሪሁን፥ የማህበረሰቡን ኑሮ ለማሻሻል የሚደረጉ ድጋፎች ቀጣይነት እንደሚኖራቸው ነው ያረጋገጡት።

በአርብቶ አደሩ አካባቢ እምቅ የግብርና አቅም ያለ በመሆኑም ከማህበረሰቡ አልፎ ለሀገር ኢኮኖሚ እድገት ማዋል እንደሚቻል የገለጹት ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ናቸው።


ይህን ሀብት በማልማት አርብቶ አደሩን ከተረጅነት ለማውጣት ሰፋፊ የግብርና ልማት ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙም ጠቁመዋል።

በአሁኑ ወቅትም አርብቶ አደሩ ማህበረሰብ ከጠባቂነት ወደ አምራችነት በመሸጋገር ሀብት በማፍራት ላይ መሆኑን ጠቁመው ፥ የሚደረገው ድጋፍም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

የደቡብ ኦሞ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ምንላርገው አዲሱ በበኩላቸው፤ በዞኑ ያሉ ሀብቶችን በማቀናጀት ለማልማት በተደረገው ጥረት ለውጥ መጥቷል።


በአካባቢው የሚገኘውን የወይጦን ወንዝ በመጥለፍ እንዲሁም የከርሰ ምድር ውሃን በማውጣት ከ 2 ሺህ 400 ሄክታር በላይ በሚሆን መሬት ላይ ሽንኩርት በመስኖ እየለማ እንደሚገኝም ነው የተናገሩት።

በዚህም ከ2 ሺህ 700 በላይ አርብቶ አደሮች እየተሳተፉ ሲሆን ማህበረሰቡን ከተረጅነት በማላቀቅ ሀብት እንዲያፈራ ማድረግ እንደተቻለም ገልጸዋል።

ከዚህ ቀደም በአካባቢው ግብርና ስራ እምብዛም እንደማይታወቅ ጠቁመው የአካባቢው ማህበረሰብ በተደጋጋሚ ለድርቅና ተያያዥ ችግሮች ተጋላጭ ይሆን እንደነበር አስታውሰዋል።


በበና-ፀማይ ወረዳ ወይጦ ክላስተር የእንጨቴ ቀበሌ አርብቶ አደር የሆኑት ተክሉ ዘውዴ እና መንግስቱ ቦንዳ ፤በኩታ ገጠም ሽንኩርትን ጨምሮ ሌሎች አትክልቶችን በማልማት ከእጅ ወደ አፍ የነበረው ኑሯቸው በእጅጉ እየተሻሻለ መምጣቱን ጠቁመዋል።


በሄክታር ከ250 እስከ 300 ኩንታል ምርት እያገኙ እንዳሉ ጠቁመው፥ የገበያ ትስስር በመፍጠር ረገድም ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑንም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ማስፈፀሚያ ከ18 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት አጸደቀ

ጋምቤላ፤ ነሀሴ 12/2018 (ኢዜአ)፡- የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ማስፈፀሚያ ከ18 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት አፀደቀ። ...

Aug 19, 2026

የአርብቶ አደሩን ማሕበረሰብ ህይወት በዘላቂነት ለመለወጥ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ስኬታማ ናቸው

ጂንካ፤ ነሐሴ 12/2018(ኢዜአ) ፡-በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኙ አርብቶ አደሮችን ህይወት በዘላቂነት ለመለወጥ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ስኬታማ መሆናቸውን...

Aug 19, 2026

የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን እያሳደገልን ነው

ጊምቢ፣ ነሐሴ4/2018 (ኢዜአ) ፡-በምዕራብ ወለጋ ዞን እየተተገበረ የሚገኘው የሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብር የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ተጨማሪ የገቢ ም...

Aug 11, 2026

በአፋር ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ 

ሰመራ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ) ፦ በአፋር ክልል የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል ...

Aug 10, 2026