የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በአፋር ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ 

Aug 10, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሰመራ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ) ፦በአፋር ክልል የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል አርባ ገለጹ።

የአፋር ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር፣ 5ኛ የሥራ ዘመን፣ 10ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ይገኛል።


ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል አርባ የክልሉን የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ለምክር ቤቱ ባቀረቡበት ወቅት እንደተናገሩት፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታማ ናቸው።

በተለይም ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን ማከናወን የተቻለ ሲሆን፤ በመስኖ ልማትም 142 ሺህ 675 ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎችና አትክልቶች መሸፈን መቻሉን ተናግረዋል።

በዚህም መሠረት በበጀት ዓመቱ ከ5 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰብ መቻሉን አብራርተዋል።

በአሁኑ ወቅት የተለያዩ የግብርና ግብዓቶች መሰራጨታቸውን አመልክተው፤ ከዚህ ውስጥም ከ47 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ ተደራሽ መደረጉን ገልጸዋል።

ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በክልሉ ያልለሙ መሬቶችን ወደ እርሻ ሥራ በማስገባት የአርብቶ አደሩና ከፊል አርብቶ አደሩን ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ማስቻሉንም ነው ያብራሩት።


በአገልግሎት አሰጣጥ ረገድ ከዚህ ቀደም ይስተዋሉ የነበሩ ችግሮችን በማስወገድ በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከ16 ሺህ በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉንም አስረድተዋል።

የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያን እስከ ታች ድረስ በማውረድና የንቅናቄ ሥራዎችን በማከናወን ከ405 ሺህ በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል።

ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል በሪፖርታቸው፤ በክልል ደረጃ 80 ሺህ 621 ዜጎች የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና መውሰዳቸውንም ነው ለምክር ቤቱ የገለጹት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፋር ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ 

ሰመራ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ) ፦ በአፋር ክልል የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል ...

Aug 10, 2026

በጉራጌ ዞን በፍራፍሬና ቅመማ ቅመም  ልማት የተሰማሩ አርሶ አደሮች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እያደገ ነው

ወልቂጤ ፤ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ በፍራፍሬ እና ቅመማ ቅመም ልማት ላይ መሰማራታችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ የጉራጌ ዞን አርሶ ...

Jul 29, 2026

አፍሪካ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ በመገንባት ዓለም አቀፍ ተደማጭነቷን ማጎልበት አለባት

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ በመገንባት ዓለም አቀፋዊ ተደማጭነቷንና ተጽዕኖ ፈጣሪነቷን ማጎልበ...

Jul 29, 2026

በክልሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ ይጠናከራል

ዲላ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ እንደሚጠ...

Jul 16, 2026