የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

አፍሪካ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ በመገንባት ዓለም አቀፍ ተደማጭነቷን ማጎልበት አለባት

Jul 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ በመገንባት ዓለም አቀፋዊ ተደማጭነቷንና ተጽዕኖ ፈጣሪነቷን ማጎልበት እንዳለባት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ገለጹ።

49ኛው የአፍሪካ ሕብረት የሥራ አስፈጻሚዎች ምክር ቤት ስብሰባ "የአፍሪካ አጀንዳ 2063ን ለማሳካት ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓት ማንበር" በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ ይገኛል።


የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የጂኦፖለቲካ ውድድር፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዎች በዓለም አቀፍ ሥርዓት ላይ ለውጥ እያመጡ ነው።

አፍሪካ የዓለምን ተለዋዋጭና ኢ-ተገማች ሁኔታ እንደ መልካም አጋጣሚ በመውሰድ ሁነቱን በራሷ መንገድ መቅረጽ እንዳለባትም ገልጸዋል።

ለዚህም አህጉራዊ ተቋማት የዓለምን ነባራዊ ሁኔታ ታሳቢ ያደረጉ ሪፎርሞችን ማድረግ እንዳባቸው ነው የተናገሩት።

ሕብረቱም በቴክኒካዊና ጥቂት ማስተካከያዎች ላይ ብቻ ሳይወሰን ስትራቴጂክና ፖለቲካዊ ውሳኔዎችን ያካተተ ጥልቅ ማሻሻያ ማድረግ እንደሚኖርበት አስገንዝበዋል።

አፍሪካ ዓለም አቀፋዊ ተደማጭነቷንና ተጽዕኖ ፈጣሪነቷን ለማሳደግ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ ሊኖራት ይገባል ብለዋል።

በዚህም አፍሪካ ለዓለም አቀፍ ችግሮች አህጉራዊ መፍትሔን በማበጀት ቁልፍ ተዋናይ መሆን እንደሚጠበቅባት ገልጸዋል።

አፍሪካ በሚያጋጥሟት ፈተናዎች መሀል ዕድገት እያስመዘገበች ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ በ2026 ፈጣን ዕድገት ከሚያስመዘግቡ 10 የዓለም ሀገራት መካከል ስምንቱ አፍሪካውያን እንደሚሆኑ ይጠበቃል ብለዋል።

የአፍሪካ ሕብረት በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ተጽዕኖ ለማሳደር ውሳኔዎቹን ማስፈጸም የሚያስችለውን ሪፎርም በማድረግ ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ ሊኖረው እንደሚገባ ነው ያመለከቱት።


የአፍሪካ ሃብቶች በአህጉሪቱ ተቋማትና ማዕቀፎች መመራት እንዳለባቸው ጠቁመው፤ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረትን የአህጉራዊ አንድነትና የጋራ ራዕይ ዋነኛ ተቋም አድርጋ ትመለከታለች ብለዋል።

ለሕብረቱ ፖሊሲዎች፣ ስትራቴጂዎችና ዘላቂ ግቦች መሳካት በትኩረት እንደምትሰራም አስገንዝበዋል።

የሕብረቱ የሥራ አስፈጻሚዎች ምክር ቤት በአፍሪካ ሕብረት የ2026 የዓመቱ መሪ ሀሳብ ትግበራና አፈጻጸም ላይ በቀረበው ሪፖርት ላይ በጥልቀት ይመክራል።

በተጨማሪም የአፍሪካ ሕብረት ስምምነቶች በፍጥነት በሚጸድቁበትና በሚተገበሩባቸው ጉዳዮች እንዲሁም በአጀንዳ 2063 ትግበራ ዙሪያ በቀረበው የኮሚቴው ሪፖርት ላይ ይወያያል ተብሎ ይጠበቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉራጌ ዞን በፍራፍሬና ቅመማ ቅመም  ልማት የተሰማሩ አርሶ አደሮች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እያደገ ነው

ወልቂጤ ፤ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ በፍራፍሬ እና ቅመማ ቅመም ልማት ላይ መሰማራታችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ የጉራጌ ዞን አርሶ ...

Jul 29, 2026

አፍሪካ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ በመገንባት ዓለም አቀፍ ተደማጭነቷን ማጎልበት አለባት

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ በመገንባት ዓለም አቀፋዊ ተደማጭነቷንና ተጽዕኖ ፈጣሪነቷን ማጎልበ...

Jul 29, 2026

በክልሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ ይጠናከራል

ዲላ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ እንደሚጠ...

Jul 16, 2026

የሩዝ ልማት ምርታማነትን በማሳደግ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ አድርጓል

መቱ ፤ ሐምሌ 2/ 2018(ኢዜአ):- የሩዝ ልማት ስራ ላይ መሳተፋችን ምርታማነትን በማሳደግ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ በኢሉባቦር ዞ...

Jul 10, 2026