የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

አፍሪካ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ በመገንባት ዓለም አቀፍ ተደማጭነቷን ማጎልበት አለባት

Jul 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ አፍሪካ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ በመገንባት ዓለም አቀፋዊ ተደማጭነቷንና ተጽዕኖ ፈጣሪነቷን ማጎልበት እንዳለባት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ገለጹ።

49ኛው የአፍሪካ ሕብረት የሥራ አስፈጻሚዎች ምክር ቤት ስብሰባ "የአፍሪካ አጀንዳ 2063ን ለማሳካት ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓት ማንበር" በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ ይገኛል።


የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የጂኦፖለቲካ ውድድር፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዎች በዓለም አቀፍ ሥርዓት ላይ ለውጥ እያመጡ ነው።

አፍሪካ የዓለምን ተለዋዋጭና ኢ-ተገማች ሁኔታ እንደ መልካም አጋጣሚ በመውሰድ ሁነቱን በራሷ መንገድ መቅረጽ እንዳለባትም ገልጸዋል።

ለዚህም አህጉራዊ ተቋማት የዓለምን ነባራዊ ሁኔታ ታሳቢ ያደረጉ ሪፎርሞችን ማድረግ እንዳባቸው ነው የተናገሩት።

ሕብረቱም በቴክኒካዊና ጥቂት ማስተካከያዎች ላይ ብቻ ሳይወሰን ስትራቴጂክና ፖለቲካዊ ውሳኔዎችን ያካተተ ጥልቅ ማሻሻያ ማድረግ እንደሚኖርበት አስገንዝበዋል።

አፍሪካ ዓለም አቀፋዊ ተደማጭነቷንና ተጽዕኖ ፈጣሪነቷን ለማሳደግ የራሷን ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ ሊኖራት ይገባል ብለዋል።

በዚህም አፍሪካ ለዓለም አቀፍ ችግሮች አህጉራዊ መፍትሔን በማበጀት ቁልፍ ተዋናይ መሆን እንደሚጠበቅባት ገልጸዋል።

አፍሪካ በሚያጋጥሟት ፈተናዎች መሀል ዕድገት እያስመዘገበች ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ በ2026 ፈጣን ዕድገት ከሚያስመዘግቡ 10 የዓለም ሀገራት መካከል ስምንቱ አፍሪካውያን እንደሚሆኑ ይጠበቃል ብለዋል።

የአፍሪካ ሕብረት በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ተጽዕኖ ለማሳደር ውሳኔዎቹን ማስፈጸም የሚያስችለውን ሪፎርም በማድረግ ዘላቂና አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ ሊኖረው እንደሚገባ ነው ያመለከቱት።


የአፍሪካ ሃብቶች በአህጉሪቱ ተቋማትና ማዕቀፎች መመራት እንዳለባቸው ጠቁመው፤ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረትን የአህጉራዊ አንድነትና የጋራ ራዕይ ዋነኛ ተቋም አድርጋ ትመለከታለች ብለዋል።

ለሕብረቱ ፖሊሲዎች፣ ስትራቴጂዎችና ዘላቂ ግቦች መሳካት በትኩረት እንደምትሰራም አስገንዝበዋል።

የሕብረቱ የሥራ አስፈጻሚዎች ምክር ቤት በአፍሪካ ሕብረት የ2026 የዓመቱ መሪ ሀሳብ ትግበራና አፈጻጸም ላይ በቀረበው ሪፖርት ላይ በጥልቀት ይመክራል።

በተጨማሪም የአፍሪካ ሕብረት ስምምነቶች በፍጥነት በሚጸድቁበትና በሚተገበሩባቸው ጉዳዮች እንዲሁም በአጀንዳ 2063 ትግበራ ዙሪያ በቀረበው የኮሚቴው ሪፖርት ላይ ይወያያል ተብሎ ይጠበቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026