የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

Sep 7, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ አስታወቀ።

በአዳማ ከተማ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል የተዘጋጀ ኤግዚቢሽንና ባዛር ተከፍቷል።


የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ሃላፊ የሺ ጂማ (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት፣ በክልሉ የዘመን መለወጫ በዓልን ተከትሎ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት አምራቹንና ሸማቹን በቀጥታ የሚያገናኝ ኤግዚቢሽንና ባዛር ተከፍቷል።

ባዛሩ ለአምራቾች የገበያ ትስስር ከመፍጠር ባለፈ ሸማቾች የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲሸምቱ የሚያስችላቸውና የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት የሚያግዝ መሆኑንም ተናግረዋል።


በአዳማ ከተማ ህገ ወጥ ንግድን በመከላከልና ምርቶች ቀጥታ ለሸማቹ እንዲቀርብ በማድረግ በኩል ያለውን ተሞክሮ ወደ ሌሎች የክልሉ ዞኖች ለማስፋፋት እንሰራለን ብለዋል።

የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሃይሉ ጀልዴ በበኩላቸው እንደገለጹት ከተማ እሰተዳደሩ የሌማት ትሩፋት መርሀግብርን ተግባራዊ በማድረግ አምራቹን ተጠቃሚ ከማድረግ ባለፈ ገበያን ለማረጋጋት ትኩረት ሰጥቶ አየሰራ ነው።


በዚህም የግብርና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግም በምግብ ራስን ለመቻልና የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ማሳደግ መቻሉን ጠቁመዋል።

የእመርታን ቀን ምክንያት በማድረግ የክልሉ መንግስት አመራሮችና የመስተዳድሩ የሥራ ሃላፊዎች የልማት ሥራዎች ጎብኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026