የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

Aug 28, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

‎በቢሮው የጥጥ ልማት አስተባባሪ አቶ ኤልያስ በላይ ለኢዜአ እንደገለጹት በክልሉ የሚካሄደው የጥጥ ልማት ከውጭ የሚገባን የጥጥ ምርት በሀገር ውስጥ ለመተካት የሚያስችል ነው።

‎‎በዚህም በተያዘው የክረምት ወቅት በክልሉ ቆላማ አካባቢዎች 75 ሺህ 717 ሄክታር መሬት በጥጥ መልማቱንና ከዚህም አንድ ሚሊዮን 945 ሺህ ኩንታል የሚጠጋ ምርት እንደሚጠበቅ ገልጸዋል።


በዚህም የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ግብ ተይዞ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።

‎ከዘር እስከ ምርት አሰባሰብ ባለው ሂደት ጥራቱን ጠብቆ ጥጥ ለማምረት እየተደረገ ያለውን ጥረት በግብርና ሚኒስቴር ስር የተቋቋመው የጥጥ ልማት ባለስልጣን ክትትልና ድጋፍ እያደረገ መሆኑን አስታውቀዋል።

‎ለአልሚ ባለሃብቶችና አርሶ አደሮች የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን በመስጠት የጥጥ ልማት ሥራው በሜካናይዜሽን ታግዞ እንዲከናወን መደረጉንም አመልክተዋል።

‎በጥጥ ልማት ሥራ ከተሰማሩት መካከል በምዕራብ ጎንደር ዞን የምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ አርሶ አደር ዘውዱ ፈቃዴ አምስት ሄክታር መሬታቸውን በጥጥ በማልማት እየተንከባከቡ መሆናቸውን ተናግረዋል።

‎‎ምርታማነታቸውን ለማሳደግና ጥራቱን ለማስጠበቅ የተሰጣቸው ስልጠና ጥራት ያለው ጥጥ በማምረት ለኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ እንደሚያግዛቸው አስረድተዋል።

‎መንግስት ለጥጥ ልማት ትኩረት መስጠቱ ሁለት ሄክታር ተኩል ማሳቸውን በጥጥ ለማልማት እንዳነሳሳቸው የገለጹት ደግሞ የዚሁ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር መከተ ገብሬ ናቸው።

‎በክልሉ ባለፈው የምርት ዘመን በጥጥ ከለማው 58 ሺህ 527 ሄክታር መሬት 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ኩንታል የሚጠጋ ምርት ለኢንዱስትሪዎች መቅረቡን ከቢሮው የተገኘው መረጃ ያሳያል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026

የአርብቶ አደሩን ማሕበረሰብ ህይወት በዘላቂነት ለመለወጥ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ስኬታማ ናቸው

ጂንካ፤ ነሐሴ 12/2018(ኢዜአ) ፡-በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኙ አርብቶ አደሮችን ህይወት በዘላቂነት ለመለወጥ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ስኬታማ መሆናቸውን...

Aug 19, 2026

የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ማስፈፀሚያ ከ18 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት አጸደቀ

ጋምቤላ፤ ነሀሴ 12/2018 (ኢዜአ)፡- የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ማስፈፀሚያ ከ18 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት አፀደቀ። ...

Aug 19, 2026