የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ ይጠናከራል

Jul 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ዲላ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ እንደሚጠናከር የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

የክልሉ የ2018/19 የመኸር አዝመራ የንቅናቄ መድረክ ዛሬ በዲላ ከተማ ተካሂዷል።


በመድረኩ ላይ የተገኙት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የዲላ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር) እንዳሉት፣ በክልሉ በተያዘው የመኸር እርሻ በቋሚና በዓመታዊ ሰብሎች ከ909 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ይለማል።

በክልሉ የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማጠናከር ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ በተያዘው የመኸር ወቅትም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

ባለፈው ዓመት የመኸር ወቅት ከ855 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በማረስ ከታቀደው በላይ ምርት ለመሰብሰብ መቻሉን አስታውሰው፣ በ2018/2019 የመኸር ወቅትም በቋሚና ዓመታዊ ሰብሎች ከ909 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ይለማል ብለዋል።

ከዚህም ከ77 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት ታቅዶ ወደተግባራዊ ሥራ መገባቱን ነው የገለጹት።

በክልሉ በ2018/19 የመኸር እርሻ ፈጥነው የሚደርሱ ጤፍ፣ ቦሎቄና መሠል ሰብሎች እንደሚለሙ የተናገሩት ኃላፊው፣ በቆሎ ማሽላ፣ አትክልት፣ ፍራፍሬ፣ ቡና፣ እንሰትና የሥራስር ሰብሎችም እንደሚለሙ አመልክተዋል።


በዞኑ ዘመናዊ የግብርና አሰራርን ተግባራዊ በማድረግ የግብርና ምርትና ምርታማነት ማሳደግ እንደተቻለ ያነሱት ደግሞ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) ናቸው።

ለዚህም በቋሚ ሰብሎች በተለይ በቡናና እንሰት ምርታማነት የመጣው ውጤት ተጠቃሽ መሆኑን አንስተው፣ ክፍት መሬቶችንም ጭምር በማልማት የመኸር እርሻን ዕቅድ ለማሳካት ይሰራል ብለዋል፡፡

በመድረኩ የክልሉ የዞንና የወረዳ ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎችና የዘርፉ ባለድርሻዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ ይጠናከራል

ዲላ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ እንደሚጠ...

Jul 17, 2026

የሩዝ ልማት ምርታማነትን በማሳደግ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ አድርጓል

መቱ ፤ ሐምሌ 2/ 2018(ኢዜአ):- የሩዝ ልማት ስራ ላይ መሳተፋችን ምርታማነትን በማሳደግ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ በኢሉባቦር ዞ...

Jul 11, 2026

በክልሉ በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም ለመጠቀም የተደረጉ ጥረቶች ውጤት አስመዝገበዋል

ሆሳዕና፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም በመጠቀም የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማ...

Jul 4, 2026

የኦንላይን አገልግሎት መጀመሩ የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባለንበት ሆነን እንድናገኝ አስችሎናል 

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/ 2018 (ኢዜአ):- ኤጀንሲው ያስጀመረው የኦንላይን አገልግሎት የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባሉበት ሆነው በቀላሉ እንዲያገኙ ማስቻ...

Jul 3, 2026