🔇Unmute
ዲላ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ እንደሚጠናከር የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
የክልሉ የ2018/19 የመኸር አዝመራ የንቅናቄ መድረክ ዛሬ በዲላ ከተማ ተካሂዷል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የዲላ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር) እንዳሉት፣ በክልሉ በተያዘው የመኸር እርሻ በቋሚና በዓመታዊ ሰብሎች ከ909 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ይለማል።
በክልሉ የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማጠናከር ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ በተያዘው የመኸር ወቅትም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
ባለፈው ዓመት የመኸር ወቅት ከ855 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በማረስ ከታቀደው በላይ ምርት ለመሰብሰብ መቻሉን አስታውሰው፣ በ2018/2019 የመኸር ወቅትም በቋሚና ዓመታዊ ሰብሎች ከ909 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ይለማል ብለዋል።
ከዚህም ከ77 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት ታቅዶ ወደተግባራዊ ሥራ መገባቱን ነው የገለጹት።
በክልሉ በ2018/19 የመኸር እርሻ ፈጥነው የሚደርሱ ጤፍ፣ ቦሎቄና መሠል ሰብሎች እንደሚለሙ የተናገሩት ኃላፊው፣ በቆሎ ማሽላ፣ አትክልት፣ ፍራፍሬ፣ ቡና፣ እንሰትና የሥራስር ሰብሎችም እንደሚለሙ አመልክተዋል።

በዞኑ ዘመናዊ የግብርና አሰራርን ተግባራዊ በማድረግ የግብርና ምርትና ምርታማነት ማሳደግ እንደተቻለ ያነሱት ደግሞ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) ናቸው።
ለዚህም በቋሚ ሰብሎች በተለይ በቡናና እንሰት ምርታማነት የመጣው ውጤት ተጠቃሽ መሆኑን አንስተው፣ ክፍት መሬቶችንም ጭምር በማልማት የመኸር እርሻን ዕቅድ ለማሳካት ይሰራል ብለዋል፡፡
በመድረኩ የክልሉ የዞንና የወረዳ ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎችና የዘርፉ ባለድርሻዎች ተገኝተዋል።
ዲላ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረው ሥራ እንደሚጠ...
Jul 17, 2026
መቱ ፤ ሐምሌ 2/ 2018(ኢዜአ):- የሩዝ ልማት ስራ ላይ መሳተፋችን ምርታማነትን በማሳደግ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ በኢሉባቦር ዞ...
Jul 11, 2026
ሆሳዕና፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም በመጠቀም የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማ...
Jul 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/ 2018 (ኢዜአ):- ኤጀንሲው ያስጀመረው የኦንላይን አገልግሎት የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባሉበት ሆነው በቀላሉ እንዲያገኙ ማስቻ...
Jul 3, 2026