የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም ለመጠቀም የተደረጉ ጥረቶች ውጤት አስመዝገበዋል

Jul 3, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሆሳዕና፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም በመጠቀም የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በተደረጉ ጥረቶች ውጤት መመዝገቡን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለፀ።

የክልሉ ግብርና ቢሮ በእንስሳትና ዓሳ ልማት ዘርፍ የተከናወኑ ስራዎችን የሚገመግም መድረክ በሆሳዕና ከተማ አካሄዷል።


በወቅቱም የቢሮው ምክትል ኃላፊና የእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ኃላፊ አቶ እያሱ ተረፈ እንዳሉት፤ በክልሉ በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም በመጠቀም የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በተሰሩ ስራዎች ተስፋ ሰጪ ውጤት ተመዝግቧል፡፡

ለአብነትም የወተት ሀብት ልማት ምርታማነትን ለማሳደግ በተደረገው ጥረት፣ ምርቱ ከቤት ፍጆታ አልፎ አሁን ላይ ስምንት የወተት ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎችን በማቋቋም የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ማሳደግ ተችሏል ብለዋል።

ለገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን በጥራትና በብዛት በማምረት ረገድ እየተመዘገቡ የሚገኙ ስኬቶች ይበልጥ እንዲጠናከሩ በትኩረት እንደሚሰራም ገልጸዋል።

በቢሮው የእንስሳትና ዓሳ ዘርፍ ልማት ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ሙሉጌታ ተስፋዬ በበኩላቸው፤ በክልሉ የእንስሳትና ዓሳ ሀብት ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችሉ ስራዎች በትኩረት እየተሰሩ እንደሚገኝ ተናግረዋል።


በእንስሳት ዝርያ ማሻሻል፣ በእንስሳት ጤና አጠባበቅ፣ በመኖ ልማት፣ በማሽነሪና በቴክኖሎጂ ሽግግር አርሶ አደሩን በህብረት ስራ ማህበራት በማደራጀት በተቀናጀ መልኩ ተጠቃሚ ለማድረግ የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

በዚህም በክልሉ በዘርፉ የተሰማሩ 57 የህብረት ስራ ማህበራትን እና ከ219 ሺህ በላይ የማህበረሰብ ክፍሎችን በቀጥታ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን አስረድተዋል።

በመድረኩ ከተሳተፉት መካከል የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋልታ የገበሬዎች ህብረት ስራ ዩኒየን ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ያሲን ሀሰን፤ ዩኒየኑ በተደረገለት ድጋፍ በዶሮ እርባታና በእንስሳት መኖ ማቀነባበር ዘርፍ ተሰማርቶ ተጨማሪ ገቢ እያገኘ መሆኑን ገልጸዋል።


ዘርፉ ያለውን አቅም ለማጠናከር የተጀመረው ጥረት ገበያን ለማረጋጋት ያስቻለ ምርት እያስገኘ መሆኑን አንስተው፣ በዚህ ዓመት ብቻ ከ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን በላይ እንቁላል ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚነታቸው እንዲጨምር መደረጉን ጠቁመዋል።

በተሰማሩበት የእንስሳት እርባታ ዘርፍ ውጤታማ እንዲሆኑ በዝርያ ማሻሻል ረገድ በተደረገላቸው ድጋፍ ስኬታማ እየሆኑ ስለመምጣታቸው የተናገሩት ደግሞ በሀዲያ ዞን የሌሞ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘሮ ዘነበች ጋርከቦ ናቸው።


በቀን እስከ 50 ሊትር ወተት ለገበያ በማቅረብ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣቱን ጠቁመው፣ በዚህም ልጆቻቸውን ከማስተማር ባለፈ ለነገ የሚሆናቸውን ተጨማሪ ሀብት እንዲያፈሩ ምቹ ሁኔታ እንደተፈጠረላቸው አስረድተዋል።

በዚህ የምክክር መድረክ መርሐ ግብር ላይ የክልልና የዞኖች የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የህብረት ስራ ማህበራት፣ ዩኒየኖችና አርሶ አደሮች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026