🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/ 2018 (ኢዜአ):- ኤጀንሲው ያስጀመረው የኦንላይን አገልግሎት የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባሉበት ሆነው በቀላሉ እንዲያገኙ ማስቻሉን ተገልጋዮች ገለጹ፡፡
አገልግሎቱ በተጀመረ አንድ ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከ3ሺህ 600 በላይ ነዋሪዎች የዲጂታል አገልግሎቱ ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ከትውልድ እስከ ሞት ያሉ ወሳኝ ኩነቶችን የሚመዘግብ ተቋም ነው፡፡
ይህንን የአገልግሎት አሰጣጡን ዲጂታላይዝ ለማድረግ ሰፊ ስራዎችን ሲያከናውን የቆየ ሲሆን፣ በቅርቡም አዲሱን ዲጂታል ስርዓት በስኬት አስመርቆ ስራ አስጀምሯል።
ይህ የቴክኖሎጂ ሽግግር ነዋሪዎች ባሉበት ቦታ ሆነው በተንቀሳቃሽ ስልካቸው ወይም በኮምፒውተራቸው አማካኝነት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል ምቹ አሰራር የፈጠረ ነው።
በኦንላይን የተጀመሩት አራቱ ዋና ዋና አገልግሎቶችም መታወቂያን ከፋይዳ መረጃ ጋር ማስተሳሰር፣ የነዋሪነት መታወቂያ እድሳትና የጠፋን መተካት፣ ያላገባ የምስክር ወረቀት አገልግሎት እና የልደት ምስክርነት ወረቀት አገልግሎት ናቸው።
ኢዜአ ያነጋገራቸው የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ፤አዲሱ የዲጂታል አሰራር ጊዜን በመቆጠብ፣ ብልሹ አሰራሮችን በመቅረፍ ትልቅ ጠቀሜታ እያገኙበት መሆኑን ነው ያረጋገጡት።
ከተጠቃሚዎች መካከል የጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ነዋሪ አቶ አባትዬ ተስፋዬ ፤ አገልግሎቱን በቀላሉ ከቤታቸው ሆነው በቴክኖሎጂው አማካኝነት ማጠናቀቃቸውን ገልጸው፣ የተዘጋጀላቸውን መታወቂያ ለመረከብ ብቻ ወደ ወረዳው መምጣታቸውን ተናግረዋል።
ይህ አሰራር ጊዜን ከመቆጠቡ ባለፈ፣ ዘመናዊና ስልጡን አሰራር በመሆኑ ከፍተኛ እርካታ እንደፈጠረላቸውም ጨምረው አስታውቀዋል።
ሌላኛው የዚሁ ወረዳ ነዋሪና የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ኢሳያስ ግርማ በበኩላቸው፤ የዲጂታል አሰራሩ ጊዜን ከመቆጠብ ባለፈ በዘርፉ ይስተዋሉ የነበሩ ብልሹ አሰራሮችን በመቅረፍ አንጻር አይነተኛ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።
ተገልጋዮች ባሉበት ቦታ ሆነው በተንቀሳቃሽ ስልካቸው ወይም በኮምፒውተራቸው አስፈላጊውን ሰነድ አያይዘው ካመለከቱ በኋላ የሚፈልጉት አገልግሎት በፍጥነት እየተሰጣቸው ይገኛል ያሉት ደግሞ በኤጀንሲው የኦንላይን አገልግሎት ባለሙያ የሆኑት ደሳለኝ ዘርጋ ናቸው።

ተገልጋዩ ወደ ወረዳ በአካል የሚመጣው የተዘጋጀውን ሰርተፊኬት ወይም መታወቂያ ለመውሰድ ብቻ መሆኑን ባለሙያው አብራርተዋል።
ሌላኛዋ የኤጀንሲው የኦንላይን አገልግሎት ባለሙያ ሶስና አወል በበኩላቸው ፤ይህ አሰራር ቀደም ሲል በወረዳዎች ላይ ይፈጠር የነበረውን ከፍተኛ የህዝብ ግርግርና የአገልግሎት አሰጣጥ ውጥረት በከፍተኛ ደረጃ እየቀነሰው ይገኛል ብለዋል።

ይህም ሰራተኞች በተረጋጋ መንፈስና በነጻነት ስራቸውን በጥራት እንዲያከናውኑ ትልቅ እገዛ ማድረጉን አክለዋል።
የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሴፍ ንጉሤ በበኩላቸው፤ አዲሱ የኦንላይን አገልግሎት አሰጣጥ በተቋሙ ይስተዋሉ የነበሩ የአገልግሎት መቆራረጦችንና የተገልጋይ እንግልትን በከፍተኛ ደረጃ እየቀረፈ መሆኑን አስታውቀዋል።

አገልግሎቱ በተጀመረ ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከ3ሺህ 600 በላይ ነዋሪዎች ከቤታቸው ሆነው በቴክኖሎጂው መጠቀም መቻላቸውን ለአብነት አንስተዋል።
የኦንላይን አገልግሎቱ በተገልጋይና በአገልግሎት ሰጪዎች መካከል ያለውን ቀጥተኛ ንክኪ በማስቀረት ብልሹ አሰራርን በጽኑ የሚከላከል መሆኑን ገልጸው፤ ይህም የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂንና ስማርት ከተማ የመፍጠር ግብን የሚያሳካ መሆኑን ዋና ዳይሬክተሩ አስገንዝበዋል።
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/ 2018 (ኢዜአ):- ኤጀንሲው ያስጀመረው የኦንላይን አገልግሎት የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባሉበት ሆነው በቀላሉ እንዲያገኙ ማስቻ...
Jul 3, 2026
አዳማ ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተቀናጀ የሰብል ጥበቃ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ግብርና ...
Jun 29, 2026
ሚዛን አማን፣ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግ...
Jun 25, 2026
ጂንካ፤ሰኔ 15/2018(ኢዜአ) ፡-የኃይለማርያምና ሮማን ፋውንዴሽን ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመቀናጀት በሚያደርግላቸው ድጋፍ ተጠቃሚ መሆናቸውን በደቡብ ኦሞ እና...
Jun 23, 2026