የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የተጠናከረ የሰብል ጥበቃ ሥራ በቅንጅት እየተከናወነ ይገኛል

Jun 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተቀናጀ የሰብል ጥበቃ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው የ2018/19 የምርት ዘመን የሰብልና ፍራፍሬ ጥበቃና እንክብካቤ ላይ ያተኮረ የንቅናቄ መድረክ በአዳማ ከተማ በማካሄድ ላይ ይገኛል።


የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ በሪሶ ፈይሳ በወቅቱ፤ በክልሉ ግብርናውን ለማዘመንና ውጤታማ ለማድረግ የተነደፉት ኢኒሼቲቮች አርሶ አደሩንና አርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ችለዋል።

ለዚህ ስኬት ደግሞ የሰብል ጥበቃና እንክብካቤ፣ የግብዓት አቅርቦት፣ የአፈር ለምነት አጠባበቅ እንዲሁም የባለሙያ ድጋፍ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማበርከታቸውን ምክትል ኃላፊው አንስተዋል።

በተጨማሪም የሰብል ልማትን በሽፋንም ሆነ በምርታማነት ዘላቂ ለማድረግ ከግብርና ምርምር ማዕከላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝም አክለው ገልጸዋል።

የሰብል ምርትና ምርታማነትን የሚጎዱ አረም፣ ተባይና በሽታዎችን በአስተማማኝ ሁኔታ ለመቆጣጠር ሳይንሳዊ መንገዶች ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑንም ጠቁመዋል።

የዛሬው የንቅናቄ መድረክም የዘርፉ አመራሮችና በየደረጃው የሚገኙ የሰብል እንክብካቤ ባለሙያዎች ይህንኑ ስኬት በጋራ ለማሳካት እንዲረባረቡ ለማስቻል ያለመ መሆኑን ተናግረዋል።

ከሰብል ጥበቃው በተጨማሪ፣ አሲዳማነታቸው የጨመረና ምርታማነታቸው የቀነሰ መሬቶችን በኖራና በተፈጥሮ ማዳበሪያ በማከም ረገድ ሰፊ ሥራ መከናወኑን ገልጸዋል።


የቢሮው የሰብል እንክብካቤ ኃላፊ አቶ ደጀኔ ሂርጳ በበኩላቸው፤ የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ከግብርና ምርምር ማዕከላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

የግብርና ምርምር ማዕከላቱ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በሽታን የሚቋቋሙ ዝርያዎችን በምርምር በማፍለቅ ለአርሶ አደሩ ተደራሽ የማድረግና ሙያዊ እገዛ የመስጠት ሥራ እያከናወኑ መሆናቸውን ለአብነት ጠቁመዋል።

ለዚህም ከዘር በፊት የሚደረግ የማሳ ዝግጅት ላይ ትኩረት የተሰጠ ሲሆን፣ ቡቃያውን ከአረሞች፣ ተባዮችና በሽታዎች ቀድሞ መለየትና መከላከል ላይ በቅንጅት በመስራት ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።

በንቅናቄ መድረኩ ላይ በየደረጃው የሚገኙ የዘርፉ አመራሮች፣ ባለሙያዎች እና የግብርና ምርምር ማዕከላት ኃላፊዎች ተሳታፊ ሆነዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የተጠናከረ የሰብል ጥበቃ ሥራ በቅንጅት እየተከናወነ ይገኛል

አዳማ ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተቀናጀ የሰብል ጥበቃ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ግብርና ...

Jun 29, 2026

በክልሉ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግባር ይጠናከራል-ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

ሚዛን አማን፣ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግ...

Jun 25, 2026

ፋውንዴሽኑ ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመቀናጀት ለስራ ፈጣሪ ወጣቶች ድጋፍ እያደረገ ነው

ጂንካ፤ሰኔ 15/2018(ኢዜአ) ፡-የኃይለማርያምና ሮማን ፋውንዴሽን ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመቀናጀት በሚያደርግላቸው ድጋፍ ተጠቃሚ መሆናቸውን በደቡብ ኦሞ እና...

Jun 23, 2026

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026