የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግባር ይጠናከራል-ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

Jun 25, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሚዛን አማን፣ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ በሚዛን አማን ከተማ ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።


የሚዛን አማን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ የ5 ኪሎሜትር ኮሪደር ልማትና የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት መስጫ መናኸሪያ ዛሬ ተመርቀዋል ።

ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት በክልሉ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ልማቶችን ማስፋፋትና ተደራሽ ማድረግ ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሠራ ነው።


በዚህ እንቅስቃሴ ውሰጥ የሕዝቡ ተሳትፎ እያደገ በመምጣቱ ትላልቅ መሠረተ ልማቶችን በመገንባት ለአገልግሎት ማዋል እየተቻለ መሆኑን ገልጸዋል።

ዛሬ ለአገልግሎት ክፍት የሆነው የሚዛን አማን መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት በቴክኖሎጂ ታግዞ ተቋማትን በማስተሳሰር ተገልጋዮችን ከብልሹ አሠራር የሚታደግ ነው ብለዋል።

መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ አቅም የሚፈጥር መሆኑን ጠቅሰው በሌሎች የክልሉ ከተሞችም ተደራሽ ለማድረግ እየተሠራ መሆኑን ጠቁመዋል።


በተመሳሳይ ዛሬ ወደ አገልግሎት የገባው የሚዛን አማን መናኸሪያ የትራንስፖርት አገልግሎትን የሚያሳልጥ መሆኑን ጠቁመዋል።

የኮሪደር ልማት ስራም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አስታውቀዋል።


የቤንች ሸኮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን በዞኑ በመንግስትና በህዝብ ተሳትፎ የተከናወኑ የልማት ፕሮጀክቶች ፍትሀዊ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ መሆናቸውን ተናግረዋል።


ለዚህም ለምረቃ የበቃውን የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎትን ለአብነት ጠቅሰዋል ።

የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢንጂነር ሰለሞን ሌዊ በከተማው የተመረቁ ፕሮጀክቶች ለሕዝብ ጥያቄ ምላሽ የሰጡ መሆናቸውን ተናግረዋል ።

የልማት ፕሮጀክቶቹ ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው መሆኑን ገልጸዋል።


ህብረተሰቡን በማሳተፍ ከተማውን ለኑሮና ለኢንቨስትመንት ምቹ የማድረግ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አመላክተዋል ።

ከከተማው ነዋሪዎች መካከል አቶ ያሲን የካ እና ወይዘሮ ጥሩዬ ከበደ በከተማው በሚከናወኑ የልማት ስራዎች ተሳትፏቸውን እንደሚያጠናክሩ ተናግረዋል ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግባር ይጠናከራል-ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

ሚዛን አማን፣ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግ...

Jun 25, 2026

ፋውንዴሽኑ ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመቀናጀት ለስራ ፈጣሪ ወጣቶች ድጋፍ እያደረገ ነው

ጂንካ፤ሰኔ 15/2018(ኢዜአ) ፡-የኃይለማርያምና ሮማን ፋውንዴሽን ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመቀናጀት በሚያደርግላቸው ድጋፍ ተጠቃሚ መሆናቸውን በደቡብ ኦሞ እና...

Jun 23, 2026

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026